‹‹ነገ ዛሬ ይሆን››

እንግዲህ ጅማሬው ከሆነ ከአንጀታችሁ ‹‹እናዳምጣለን….ንገሩን›› ካላችሁ… የይስሙላ፣ የእድሜ ማራዘሚያ፣ የጥገና እና ተንፏቃቂ ለውጥ አንፈልግም። ጉልቻው እንዲቀያየር፣ ሽንቁር የበዛበት ግድግዳ ቀለም ፣ አሳማው ሊፕሰቲክ እንዲቀባ አንሻም። ባረጀ እና ያፈጀው ‹‹ተሃድሶ›› ሀረግ ዳግም መደለል፣ ዳግም መታለል አንፈልግም። የ‹‹ተጨፈኑ ላሞኛችሁ›› ፖለቲካ አንገሽግሾናል። የዘመናት‹‹እድሳትማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹እድሜ ለግንቦት ሃያ…››

በግንቦት 20 ዋዜማ ዋልታ ቴሌቪዥንን እያየሁ ነው። ጋዜጠኛው ዝግጅቱን ከአመት አመት በማይቀየሩት መፈክሮች( ለምሳሌ “ግንቦት 20 የህዝቦች ሁሉ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ ያገኘበት ቀን ነው) ጀመረና፣ ዛሬም በጭንቅላቴ ውስጥ የሚፈነጩትን ጥያቄዎች ዘርዝሬ ለማሰብ እንኳን እድል ሳይሰጠኝ፣ “ከግንቦት 20 ወዲህ የተወለዱ ልጆችማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹ገዳዬ…ገዳዬ…››

(መነሻ ሃሳብ፤ የሞፋሳ (ኬንያዊ ገጣሚ) ‹‹ልጅቷ›› ግጥም) ፀሐያቸው ጠልቃ በሰው ሀገር መሽቶብኝ ነበር። ጨልሟል። የተለመደውን አውቶብሴን ተሳፈርኩ። አዲስ ነገር የለውም። ሁሌም የምጠብቀው፣ ሁሌም በጠበቅኩት ሰአት የሚመጣው የማይዛነፍ የእለት ውሎዬን የሚደመድመው አውቶብስ ነው። እንደተቀመጥኩ፣ ሰንደቅ የሚያሰቅል ቁመት ያለው ውብም፣ ሎጋም ኢትዮጵያዊማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹አላቅሱኝ››

ትላንት አባቴ ሞተ። ካሁን በኋላ በለመድናት ሰአት የውጪ በራችንን በቁልፉ ‹‹ቃ›› አድርጎ ከፍቶ ላይገባ፣ ካሁን በኋላ ሳመሽ በረንዳ ላይ ጋቢውን ለብሶ እሳት ጎርሶ ጠብቆ ላይቆጣኝ፣ ካሁን በኋላ የአመት በአል ድፎ እየሳቀ ላይቆርስ፣ ካሁን በኋላ ልጄን፣ የልጅ ልጁን አቅፎ ላይስም… ሞተ።ማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹የሪል እስቴት ማላገጫዎች››

አሁንስ እነዚህ ኑሮ እጅ በጆሮ ያስያዘው ምስኪን ሕዝብ ላይ በይፋ የሚያላግጡ የሪል እስቴት ማስታወቂያዎች ቃር ሆኑብኝ። አነፈሩኝ። መቼስ፣ በለስ ቀንቶት፣ ወርሶ ወይም ከመንግሥቱ ነዋይ ግርግር ጀምሮ ቆጥቦ እዚህ ለደረሰ የናጠጠ ሃብታም ማስተዋወቃቸውን አልቃወምም። እነዚህ በሌላ የተንጣለለ እልፍኛቸው እየኖሩ ማስታወቂያውን የሚመለከቱማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹ተዘጋጂ፤ ግን አትሂጂ››

ይህች መናጢ ግብፅ ከኤርትራ ጋር ተሞዳሙዳ፤ ‹‹አንድ ቀን ታርቀን ቤት ሰርተንበት በአብርሃም አፈወርቂ እና በቴዲ አፍሮ ዘፈን አብረን እንጨፍርበታለን›› ያልነው ዳህላክ ላይ የጦር ቤቷን መገንባት ጀመረች አይደል? ግብፅም፣ አዲሷም ተኝተውልን አያውቁምና ነገሩ ብዙ ባይደንቅም ክፉኛ ያስተክዘኝ ገብቷል። የሚያምሰን ነገር በዝቶማንበብ ይቀጥሉ…

ዘውድም እነሱ ጎፈርም እነሱ

ቀምጣላ ስድስተኛ ቤቷን በአዲስ አበባ የገዛችው ዘመን ያገነነናት ሙሰኛ የድሮ የትምህርት ቤት ጓደኛዬን ካገኘሁ ወዲህ የአርባ-ስልሳ ነገር ያነደኝ፣ የኮንዶሚኒየም ኪራይ ያንጨረጭረኝ ጀምሯል። ልጅቱ አንድ ኮንዶሚኒየም፣ አንድ የሰንሻይን ሪል ሰቴት አፓርትማ፣ አንድ የፍሊንትስቶን ሆምስ ታወን ሃውስ፣ አንድ የማህበር ቤት፣ አንድ ሰበታማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹ኑ! አንድ ቤት ግቡ!››

መስሪያ ቤቴ ሁለት የከፍተኛ መደብ ልጆች ብቻ የሚማሩባቸው ትምህርት ቤቶች መሃከል የተሰነገ ነው። ጠዋት ሲገቡ፣ እረፍት ሲወጡ፣ ማታ ሲሄዱ አያቸዋለሁ። ከወዛቸው፣ ከቀብራራነታቸው፣ አማርኛን ከደቆሰው እንግሊዝኛቸው ጎልቶ የሚታየኝ፤ መጀመሪያ የሚቀበለኝ ዘወትር ዳንኪራ የሚረግጡበት አደንቋሪ፣ ተንጫራሪ ራፕ ሙዚቃቸው ነው። የነ ድሬክ፣ የነማንበብ ይቀጥሉ…

ሳይወለድ ሞተ

ከሌሊቱ ሰባት ሰአት ገደማ። ተኝቼ ነበር። ህመም አልነበረኝም። ያው ከተለመደው ማቅለሽለሽ ያለፈ ያስጠነቀቀኝ፣ ለዚህ ልብ ስብራት ያዘጋጀኝ ህመም አልነበረኝም። ብቻ ስደማ ተሰማኝ።…ቀስም ቶሎ ቶሎም የሌሊት ልብሴ ላይ፣ አንሶላው ላይ ስደማ ተሰማኝ። ተደናብሬ የራስጌ መብራቱነ አበራሁት። ልብሴም፣ አንሶላውም ደም በደም ሆኗል።ማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹ማርች ኤትን በአዝማሪ››

ሁለት መቶ ሰው ፊት መስሪያ ቤታችን ለሚከበረው የአለም የሴቶች ቀን ዝግጅት አስተባባሪ ሆኜ ስሾም ይህንን ቀን ‹‹ማርች ኤጭ›› እያሉ የሚጠሩት ወንዶች ባልደረቦቻችን እና እኛንም የማያማርር ‹‹ሴቶች ለሴቶች የሚያዘጋጁት አሰልቺ ቀን›› ፣ ሴቶች አበሻ ቀሚስ ለብሰው ፈንዲሻ እየበሉ ወንዶችን የሚረግሙበት ቀን››ማንበብ ይቀጥሉ…