“ሁ ኢዝ ባድ?!”

ይህቺ ጭዌ ከዚህ ቀደም ተፖስታ የነበረ ሲሆን ሰሞኑን ከሚከበረው የአጼ ሚኒሊክ ልደትና የጠ/ሚ መለስ ሙት አመት አንጻር ለሁለቱም ቀደምት መሪዎች ወዳጅም ሆነ ጠላት ሚዛናዊ ነው በሚል በአድማጭ ጥያቄ በድጋሚ የቀረበች ነች።ጽሁፉ ትንሽ ረዘም ይላል ያው የምታነቡት ካጣችሁ ብቻ ተደበሩበት። መቼቱማንበብ ይቀጥሉ…

የአርሲ ዐጃኢባት

እኛ (እደግመዋለሁ “እኛ”፣ “ኑቲ”፣ “ናህኑ”) የኢትኖግራፊ ፈረሳችንን ተሳፍረን ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ፣ ከመሀል እስከ ሰሜን መጋለብ ሱስ የሆነብን ጸሐፊ ከሀረር መሆናችንን ታውቃላችሁ አይደል? ታዲያ እኛ (አሁንም እደግመዋለሁ “እኛ”) ወደ ሌሎቹ ስፍራዎች ስንጋልብ የነበረው ከሌሎች አካባቢዎች ሁሉ የሚቀርበንን አንድ ጎረቤታችንን እያለፍን ነው።ማንበብ ይቀጥሉ…

እድሜዬ እና የኢትዮጲያ እርምጃ!

ሰላም ነው ጋይስ! እንግዲህ ቅዳሜ እለት በከፍተኛ ድምቀት ተከብሮ ያለፈውን የ 35ኛ አመት የልደት በአሌን በማስመልከት ብዙዎች ” እድሜህ ስንት ነው?” በማለት በጠየቃችሁት መሰረት ስለ እድሜዬ የሚከተለውን መግለጫ ለመስጠት ተገድጃለሁ። ግና ለአንባቢ የተወለድኩበትን ዓመተ ምህረት በቀጥታ ከመናገር ይልቅ እስከዛሬዋ እለትማንበብ ይቀጥሉ…

ከጊቤ ባሻገር ያለችው ጅማ (ክፍል ሁለት)

እነሆ ከተሚማ ጋር የጂማን ምድር “ሽርርርር” እያልንበት ነው። ሆኖም “ተሚማ” የትናንትናው ሙገሳ አንሶኛል ብላለች። “የነየታችሁት ሐጃ ሞልቶላችሁ በደስታ እንድትፍለቀለቁ ካሻችሁ ሙገሳውን ጨመርመር አድርጉልኝ” ትላለች። ታዲያ እኛም አላንገራገርንም። “ምን ገዶን! አንቺ ሰኚ ሞቲ! ሙገሳ በየዓይነቱ ይኸውልሽ” ብለን በድጋሚ መወድሳችንን ልንደረድርላት ተዘጋጅተናል።ማንበብ ይቀጥሉ…

መረራ ጉዲናን ሳስታውስ

በ1988 የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና (ESLCE) እንደወሰድኩ ነው። ዕለቱ ከሚያዚያ ወር መአልት አንዱ መሆኑ ይታወሰኛል። በዚያች ዕለት የጀርመን ድምጽ ራድዮ ከቀደሙት የኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተለየ ዓላማን ያነገበ ድርጅት መቋቋሙን ዘገበ። የድርጅቱ መስራች የሆኑት ግለሰብ የተናገሩትንም ቀንጨብ አድርጎ አስደመጠን። በጉዳዩ ዙሪያማንበብ ይቀጥሉ…

ከጊቤ ባሻገር ያለችው ጅማ!

በለምለሚቷ ምድራችን ላይ እየተሽከረከረ ዚያራ ማድረግ ወጉ የሆነው የኢትኖግራፊ ፈረሳችን ታሪካዊቷን ጅማንና ህዝቧን መጎብኘት አሰኘው። እኛም “አበጀህ! ጥሩ ሀገር መርጠሃል” በማለት መረቅነው። ፈረሳችንም የደቡብ ምዕራብ አቅጣጫን ይዞ ገሰገሰ። ከጊቤ ዉሃ ከተጎነጨ በኋላም ወደ ታሪካዊቷ ቀበሌ ሰተት ብሎ ገባ። ጅማ! የአባጅፋርማንበብ ይቀጥሉ…

ወለጋ እና ሌንሳ ጉዲና

ከዚህ በፊት ስለወለጋ የሚያትት አነስተኛ ጽሑፍ በዚህ ግድግዳ ላይ ለጥፌ ነበር። ይሁንና ያቺ ጽሑፍ ለወለጋ ክብር የምትመጥን አልመሰለኝም። ብዙ ድርሳናትን ለሚያስጽፈው ምድር ትንሹን ብቻ እንደ መወርወር ነው። በመሆኑም በዛሬው የኢትኖግራፊ ጉዞአችን ወለጋን ደግመን ልንዘይረው ተዘጋጅተናል። ጉዞ ወደ ምዕራብ ኦሮሚያ! ዳይ!ማንበብ ይቀጥሉ…

የኢትኖግራፊ ጉዞ ወደ ጎጃም (ክፍል ሁለት)

ጎጃምን ከሌሎች የቀድሞ ክፍለ ሀገሮቻችን ለየት የሚያደርገው ዙሪያውን በዐባይ ወንዝ የታጠረ መሆኑ ነው። ከጣና ሐይቅ በስተምዕራብ ራቅ ብሎ ካለው የግልገል ዐባይ መነሻና በሱዳን ድንበር መካከል ከሚገኘው ክፍት መሬት በስተቀር ክፍለ ሀገሩ በሙሉ በዐባይ የተከበበ ነው። እርግጥ በወንዝ የታጠሩ ሌሎች ክፍለማንበብ ይቀጥሉ…

የኢትኖግራፊ ጉዞ ወደ ጎጃም

ያ በእውቀቱ ስዩም የሚሉት ጎጃሜ ብላቴና አምናና ዘንድሮ የኛዋን ኦሮሚያን በብዕር መነካካቱን አብዝቷል። እስከ ዛሬ ድረስ “ይሄ ልጅ ለምን አያርፍልንም? እኛም እርሱን ስላፈራችው ጎጃም መጻፍ የማንችል መሰለው እንዴ” እያልን ከራሳችን ጋር ስንነጋገር ቆይተናል (“እኛ” ወልደ-ገለምሶ ዘብሔረ ሀረርጌ በመሆናችን ባሰኘኝ ጊዜማንበብ ይቀጥሉ…