ውይ መፅሐፍ ቅዱስ…

1. “ወደ እኔ የሚመጣ ሊከተለኝም የሚወድአባቱንና እናቱን፣ ሚስቱን እና ልጆቹን፣ወንድሞቹንና እህቶቹን፣ የራሱንም ሰውነት እንኳ ቢሆን የማይጠላ ደቀመዝሙሬ ሊሆን አይችልም” ሉቃ. 13፣33 እንደው ይቅርታ አድግልኝና እየሱስ፣ እንኳን እናትና አባቴን አሁን ታይፕ የማደርገውን ፅሁፍ እንኳ ትቼ ልከተለህ አልችልም፡፡ ካንተ በፊት እናትና አባቴን…ማንበብ ይቀጥሉ…

የእንባ አውራ ጎዳኖች

ይሄውልሽ እምዬ፡- በሆዴ የያዝኩት የብሶቴ ክምር ብዙ ሲናገሩት-አብዙት ሲፅፉት፣ መስሎሽ ባዶ `ሚቀር- እንዳትታለዪ ይብሱን ነው `ሚያድግ፣ እጅጉን ነው `ሚንር ይቀለኛል ብዬ በነገርኩሽ ቁጥር፡፡ ከወደቁ ኋላ መፈረጋገጡ፣ ውጤቱ መላላጥ እንደሆን አውቃለሁ ግን ከዝም በላይ አይጎዳኝምና ስሚኝ ነግርሻለሁ! እዚህ ካንቺ ግቢ፣ እዚሁማንበብ ይቀጥሉ…

የሴቶች ካቴና!

ይህች ፅሁፍ ባለፈው ዓመት “በአዲስ አድማስ” ጋዜጣ ላይ ወታ ነበር፡፡ በጊዜው ትንሽ ተነካክታ ስለነበር ኦርጅናል መልኳን እንዲህ አቅርበናል፡፡ የሴቶች ካቴና! ሰልችተውኛል፡፡ አንዷ ከአንዷ በቁመት፣ በመልክ፣ በሰውነት ቅርፅ ቢለያዩ እንጂ በአዕምሮ አንድ ሆነውብኛል፡፡ ብዙ ሴቶችን አይቻለሁ፡፡ ያው ናቸው፡፡ ለፍቅር ስሱ ነኝ፡፡ማንበብ ይቀጥሉ…

እኛ ማን ነን…!

አውቀን የተኛን ነን፡፡ ቢቀሰቅሱን የማንሰማ! ከከተሳካልን ቀስቃሾቻችንንም አሰልችተን የምናስተኛ! …ሰውነታችን ጣምኖ ጮማ ከምንቆርጥ ይልቅ፣ ያለምንም ልፋት የምናገኛትን ጎመን እየላፍን፣ “ጎመን በጤና” የምንል ዘመናዮች ነን፡፡ ታሪክ ዳቦ አይሆንም ብለን፣ ታሪክ የማይሆን ዳቦ እየገመጥን ያለን በልቶ አደሮች ነን፡፡ ነፃታችንን ከባርነት እግር ስርማንበብ ይቀጥሉ…

ስለ ሴቶች

ተከርክሞ የተገረበ፣ ቧልትና ቁምነገር!! “ስለ ሴቶች“ ( ስለ ወንዶች ደግሞ እነሱ ይፃፉ) ከአፈጣጠር እንጀምር፤ በኔ እምነት፣ ሴቶች የተፈጠሩት፣ ወንዶች በተፈጠሩባት ቅፅበት ነው፡፡ እንደ መጥሐፉ ከሆነ፣ ሴት የተፈጠረችው ሁለተኛ ነው፡፡ በደንብ ካየነው ግን እኩል ነው የተፈጠሩት፡፡ ወንድ ሲፈጠር፣ እንትን ነበረው አይደል?ማንበብ ይቀጥሉ…

ለሀገሬ፣ ለሃይማኖቴ፣ ለአላማዬ አልሞትም!!!

ለምን ዓላማ እና ለማን ዓላማ ለመሞት ዝግጁ ናችሁ? ለአላማ መሞት አሪፍ ነገር ነው አይደል? አዎ! አሪፍ ነው ለብዙኀኑ- በግሌ ለኔ አይደለም፡፡ በያዝኩት ነገር ምክንያት ሞት ከመጣብኝ፣ ምላሴን አውጥቼበት ላሽ እላለሁ እንጂ፣ የሞኝ ጀብደኛ ሞት አልሞትም፡፡ በመሰረቱ አላማ የለኝም ቢኖረኝም ሙትልኝማንበብ ይቀጥሉ…

ሞት እኩል ይሆናል ሕይወት

ሞት = ህይወት ‘‘የሞት እንቆቅልሽ የሚመስጠን፣ የማይቀር፤ ነገር ግን የማናውቀው ነገር በመሆኑ ነው’’-(አፍሮጋዳ) የ“አምላክ” ትልቁ ጥበቡ ሞትን መፍጠሩ ነው- ለኔ! እያንዳንዱ ሃይማኖት እግሩን ያቆመው በሞት ላይ ነው። ሞት ባይኖር የሰው ልጅ፣ በአምላክ አማኝ አይሆንም።ሃይማቶች እግር ይከዳቸዋል። …ዘር ካልሞተ/ካልበሰበሰ ፍሬ አይሆንም።ማንበብ ይቀጥሉ…

የማንን ሃሳብ፣ በማን ጭንቅላት እያሰባችሁ ነው?

የማንን ሃሳብ፣ በማን ጭንቅላት እያሰባችሁ ነው? ( ብዙ ጭንቅላቶች ቢኖሩም፣ ብዙ ሀሳበች የሉም) የሰው ልጅ አሳቢ ፍጡር ነው ቢባልም አብዛኛው ግን አይደለም፡፡ ብዙሃኑ ታስቦ ያለቀ አሳብ እራሱ ላይ ጭኖ የሚሄድ መንገደኛ ነው፡፡ ግቡ መሄዱ እንጂ መድረሱ አይደለም፡፡ “ለምን” የሚባል ጥያቄማንበብ ይቀጥሉ…

ሀገሬ ታማለች!

ታማሚ የመሆንሽን እውነት፣ ስታውቂው፣ ሳውቀው ሳይርቀን፣ ለምን ነው፣ ይህ አባይ ቃልሽ እውነቱን የሚደብቀን? ልንገርሽ አይደለ እውነት…. እንዳንቺም ታማሚ የለ በምድር የተስተዋለ አንድነት ቁስል ሆኖበት ልዩነት ደዌ ፀንቶበት፣ መንገዱን ለሞት ያበጀ ፍፃሜን በራ ያወጀ እንዳንቺም ታማሚ የለ፣ በምድር የተስተዋለ፡፡ ግራሽን ለመታማንበብ ይቀጥሉ…

ላኩኝ የማይል ደብዳቤ!

አምላክ ሆይ! ይህንን የምፅፍልህ፣ ከአመት ለማታልፍ ፍቅረኛ በውሸት በኮሹ፤ በቆሸሹ ቃላት ከምቸከችከው ውዳሴ ከንቱ የተሸለ መሆኑን አምኜ ነው፡፡ የእውነት አምላክ ነህና የምትወደው እውነትን ነው፡፡ ስለዚህ እቅጭ እቅጯን እናወጋለን፡፡ ሃሳቤን ለሰዎች ባወጋቸው በአንተ ያምኑ ይመስል፣ ደም ስራቸውን ገትረው፣ ዐይናቸውን አፍጠው ይከራከሩኛል፡፡አንተማንበብ ይቀጥሉ…