ዕውቀት ይቅደም

” . . . ዕውቀት ይቅደም ነው ያልኩት። ያውም ሰፊ ዕውቀት። ከአትኩሮት ጠባብነት እንውጣ ማለቴ ነው። ከደቃቃዊነት (Minimalism) ወይም አሹራዊነት (ከአስሩ አንዱን ብቻ ማየት) መሸሽ ነው። በሌሎች ሃገሮች እዚህ ‘ቀይ ሌሊት’ ዐይነት ስራ ከመድረሳቸው በፊት ታላላቅ ስራዎች ተደጋግመው ተሰርተዋል። ድልድዩማንበብ ይቀጥሉ…

(ሕልም)

የሕልም ዓይነት አለ፡ እየጮሁ መጮህ የማይችሉበት፣ እየሮጡ መሮጥ የማይችሉበት፣ እያለቀሱ ዕንባ የማያወጡበት። ሕልምም አለ፡ የማያልቅ የማያልቅ መንገድ የሚጓዙበት…… ሕልምስ አለ የዘለቃ ባነው እንኳ የሚወቃ (ዘለቃ አስቀያሚ በመሆኗ) ሕልምስ አለ የነ አልማዝ ከወር እወር የሚያፈዝ (ደደብ ስለሆኑ አልማዞች) ሕልምስ አለ የመዘዞማንበብ ይቀጥሉ…

…ምስክሬ ነው

ወላጅ አባቴ በእናቴ አሳቦም ይሁን አስመርራው ሸሽቶኝ ቢሄድም ይሄ ዓላዛር የተባለ የሽሮሜዳ ሸንኮራ እግሮቼን ተከትሎ ወደምሄድበት ሄደ፥ አረፍኩበት አረፈ፥ ሳቄን ሳቀ። አባቴ ወደ ቆላ ቢኮበልልም ዓላዛር እጄን ያዘኝ። ዘመናይ ለዘመናይ። እዚህች ደጋና ወይና ደጋ ሰላሜን አገኘኋት፥ አዚዬ በቁጭት የተጨበጠች ግራማንበብ ይቀጥሉ…

ጩጬ ብንሆንም ይገባናል

ምሽቱ ለዓይን ሲይዝ ቤታችን ፊት ለፊት በሩን ራቅ ብዬ እያየሁ ወዲያ ወዲህ እላለሁ፡፡ የሰፈሩ ልጆች ሁሉ በየቤታቸው ገብተው እኔ በዛ ቀዝቃዛ ምሽት አስፋልት ዳር ቀጠሮ እንዳለው ሰው ወዲያ ወዲህ እላለሁ፡፡ ቤቴ አልገባም፡፡ ታዲያ ወላጆቼ እኔን መጠበቅ ይሰላቹና..…. እናቴ ኩታዋን ተከናንባማንበብ ይቀጥሉ…

የመዲባ ኡሪ

ከዕለታት አንድ ቀን ‘ጣይቱ’ የተባሉ እተጌ እዛች ፍልውሃ የምትባለው የምትጤስ ቦታ፣ እዛች እርጥብ ፊንፊኔ ገላቸውን ተጣጥበው ጨርሰው፣ ከተቀመጡበት በርጩማ ብድግ ሲሉ፣ እንደ ደንግ የምታበራ የሕልም እንቁላላቸው የምትሞቅ ግልገል ኩሬ ውስጥ ወደቀች፡፡ ከዛም ወደ ተሰራላቸው ማረፊያ ጎጆ አቀበቱን ሲያዘግሙ፣ ስሟ የተጠራማንበብ ይቀጥሉ…

ለፅጌሬዳ ሐብታሙ

‹‹እንደ አንቺ አንድ ቦታ የበቀልኩ ባሕር ዛፍ ሳልሆን እንደ ኮባ ውላጅ የተሸከረከርኩ ነኝ፡፡›› 03/07/79 ለፅጌሬዳ ሐብታሙ ፓ.ሣ.ቁ 0000 አዲስ አበባ ለጤናሽ እንደምን ከርመሻል? ሦስት ሳምንቶች ያህል ከጠፋሁብሽ በኋላ በዐይነ ስጋ ሳይሆን—እንዲህ በወረቀት፣ በቀለም፣ በሆሄያት፣ በፓስታ ላናግርሽ መሆኔ ግራ ሳይሆንብሽ አይቀርም፡፡ማንበብ ይቀጥሉ…

ጉድጓዱና ውሃው

አንዳንዴ እያካፋ…… አዲስአባ ቀላል ደመና ተከናንባ…… እንደ ነጠላ…… ሲያካፋ፣ ፀሐይም…… ፀሐይ ከራ ወበቅና የቀዝቃዛ አየር እጥረት እግሮቼን አሳስሮአቸው ያጋጠመኝ ቦታ ተቀምጬ አገጬን እጆቼ ላይ አስደግፌ ሳስብ፣ ሕሊናዬ በእጅና በእግሩ እየዳኸ፣ እየወደቀ፣ እየተነሳ ወደ ንፋስ መውጪያ ይነዳኛል፡፡ ብጠላውም፣ ተዘርቼ የበቀልኩበትን ብጠላውምማንበብ ይቀጥሉ…

ፀጥታ ነጋሲ

ይኼ አብኛዛውን የምንኖርበት አለም ፀጥታ ነው፡፡ ያልተነገረለት ነው፡፡ ሆሄ፣ ቃል፣ አንቀፅ፣ ምዕራፎች፣ ቅዳሴና ዘፈን፣ እንጉርጉሮና ምንትስ አልተነዳበትም የሚባል፡፡ ምድር ላይ ከተሰሩና ከተደረጉ ከታሰቡና ከታለሙ ነገሮች የተመዘገበው ስንቱ ነው? የአዳም የመጀመሪያ ሳቁ ተመዝግቧል? የመጀመሪያው የአዳም ወይ የሄዋን እንጉርጉሮ ይታወሳል? የሐጢያት መጀመሪያማንበብ ይቀጥሉ…

ኩልና ተኮላ

ተኮላ የተባለ ሰው አፍቅሬ በትዳር መኖር ከጀመርኩ አሁን ሰማንያ ሰባት ነው አይደል? አዎ አንድ አመት ተኩል አለፈኝ፡፡ በዚህ …. ማለት በቃ ከእሱ ጋር አንድ ቤት ውስጥ ሚስቱ ሆኜ በመኖሬ ደስተኛ ነኝ፡፡ አንዳንድ ሰዎች በማያገባቸው መግባት የሚወዱ ወይም የማናቀፍ ጉጉታቸው ወሰንማንበብ ይቀጥሉ…

ቡቡ ዘተበሃለ ስንዝሮ (ከ “የስንብት ቀለማት” የተወሰደ)

ተረት ተራች ነኝ፡፡ ድሮ ድሮ እንደ እኔ አይነቱ ተራች፣ ጉዳይ ቀማሚ ፣ የታሪክ ጉድፍ ነቃሽ ‹ሐዳሚ› ይባል ነበር፡፡ በጥንት አፍ እንግዲህ ሐዳሚ ነኝ፡፡ ህይወት ተወሳስባ፣ ተተረማምሳና ተሸፋፍና ልታልፍ ስትል ለአፍታ ጆሮዎ ስር አቆማትና በአንደበቴ (በልሳነ ጥንት፣ በልሳነ ድንጋይ ዘመን ቀባጢሶ)ማንበብ ይቀጥሉ…