እይታና ምዘና

በዚህ አለም ላይ ፤እንደ ወንድ ልጅ ጨካኝ ፍጡር አለ? ወንድ ልጅ በወንድ ልጅ ሲጨክን ለከት የለውም፤ባለፈው ከስንት ጊዜ በሗላ ፎቶ ለመለጠፍ ወሰንኩ። የሃይሌ ገብረስላሴን ያክል እንኳ ያክል ባይሆን፤ የሃይሌ ገሪማን ያክል ሮጨ፤ እምብርቴን የወጠረውን የጮማ አሎሎ አቅልጨ፤ ሰው ፊት የሚቀርብማንበብ ይቀጥሉ…

የሚቀጥለው ፋሲካ

(የሚያስተክዝ ትዝታ) ያኔ ልጅ እያለሁ ፤ የፍልሰታ ጦምን እስከዘጠኝ ሰአት እፆም ነበር። የፆም አላማ ፤ወደ እግዚያብሄር ለመቅረብ፤ በረከት ለማግኘት እና ሀጢአትን ለማስተረይ እንደሆነ ይታወቃል ። እኔ ግን የምጦመው በፆም ወቅት ቤት ውስጥ ምግብ ስለማይሰራ ነው፤ ጦሙ ሊገባ ሁለት ቀን ሲቀረውማንበብ ይቀጥሉ…

አንጀት የመብላት ጥበብ

የሆነ ጊዜ ላይ የሚሰራበት መስርያ ቤት፤ ለዓለምአቀፍ ስብሰባ ወደ ውጭ ሀገር ላከው:፤ በተላከበት የፈረንጅ ከተማ ሆቴል ውስጥ ፤ አንድ ሳምንት በስብሰባ ዛገ፤ እናም፤ ያንቀላፋ ልቡን የሚቀሰቅስለት አንድ ነገር ፈለገ፤ አንድ ቀን ሆቴሉ አጠገብ የሚገኝ ቡና መጠጫ ቤት ውስጥ ገባ። ካፌውማንበብ ይቀጥሉ…

ሆሆ

“ወንድ ሆኖ የማያመነዝር ፤ ወታደር ሆኖ እማይሰነዝር ፤ ነጋዴ ሆኖ እማይዘረዝር የለም ! “ይላል ምኡዝ። እውነቱን ነው፤ከጥቂቶቻችን በቀር ብዙ ወንድ በህይወቱ ቢያንስ አንዴ በትዳሩ ላይ ያድጠዋል። ድርያ በአርቲስት ላይ ይጋነናል እንጂ ፊትና ጭን ከተሰጠው፤ ገበሬ ነጋዴ ፓስተር ሼህ የንስሃ አባትማንበብ ይቀጥሉ…

እንደማመጥ

እድሜየ ላቅመ ምክር ስለደረሰ ልመክር ነው፤ ስልጣንህን ተጠቅመህ የተወዳዳሪህን የመናገር ነፃነት ስታፍን ፤ራስህንና አገርህን በሁለት መንገድ ትበድላለህ። አንደኛ ልክህን እንዳታውቅ ትሆናለህ! ዜጎች ባስተዳደርህ ላይ የሚያቀርቡትን ቅሬታ ካልሰማህ እንዴት ልክህን ታውቃለህ? ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው፤ብዙ አምባገነኖች የወዳጆቻቸውን ከንቱ ውዳሴ የህዝብ ድምፅማንበብ ይቀጥሉ…

መርታት፤ መረታት፤ መገገም

የሆነ ጊዜ ላይ ረከቦት ጎዳና፤ ባንዱ ካፌ ውስጥ፤ ቡና ስጠጣ፤አንድ ጎረምሳ ወደ ተቀመጥኩበት መጣ፤ልጁ ግድንግድ ነው፤ጎልያድ ዳዊትን አዝሎ ያክላል፤ እኔ ደሞ እንደምታውቁኝ ነኝ፤ከፊቴ ሲቀመጥ የሚጥሚጣ ብልቃጥ አከልኩ፤ ግብዳው ብዙ ሳይቆይ የምነት ክርክር ጀመረ፤በተቻለኝ መጠን ወደ ክርክሩ ላለመግባት ተግደረደርኩ፤ ሰውየው ግንማንበብ ይቀጥሉ…

የማብራትና ማጥፋት ወግ

(የመጨረሻው ክፍል) ባገራችን፤ በባላባት ስርአት ወግ “ፈናወጊ “ የተባሉ አገልጋዮች ነበሩ፤የስራ ድርሻቸው ፋኖስ፤ አንዳንዴም ጡዋፍ ይዞ መቆም ነበር፤ራት ላይ ከጌቶች እና ከእመቤቶች ማእድ ትንሽ ፈንጠር ብለው ቆመው ያበራሉ፤ በቤተመንግስት ውስጥ መብራት ተሸክመው የሚያነጉም ነበሩ፤የመጀመሪያዎቹ የመብራት ምስሶዎች ነበሩ ማለት ይቻላል፤ ታድያማንበብ ይቀጥሉ…

የመብራት የመጥፋት ትዝታ፤ከባለፈው የቀጠለ

ከጥቂት አመት በፊት የረር በር እኖር ነበር፤አንድ ቀን መብራት በጊዜ ጠፋ፤እስከ እኩሌሊት ድረስ ስላልመጣ ተስፋቆርጠን ተኛን፤ ዘጠኝ ሰአት ላይ ሚስቴ ቀሰቀሰችኝና ወደ ምኝታቤቱ መስኮት ጠቆመችኝ፤ የሆነ ግዙፍ እጅ ጥላ መስኮቱን ሲዳብስ ይታየኛል፤ “ሌባ ነው?” አልኩዋት፤ ራሱዋን ባዎንታ ወዘወዘች፤ “መስኮቱን ምንማንበብ ይቀጥሉ…

ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ባለስልጣን ጋር በመተባበር የተቀሰቀሰ ትዝታ

ወደዚች ምድር ስመጣ ማንኩሳ በጭላጭ ኩራዝ ተቀበለችኝ፤ ኩራዙ ያራት ነገሮች ጥምረት ነው፤ የኮኮስ ቅባት ጠርሙስ፤ በምስማር ተበሳ ቆርኪ፤ የዝሃ ክር እና ላምባ። በጊዜው የኩራዝ ማብሪያ መቅረዝ አይታወቅም፤ ከያንዳንዱ ጎጆ የውስጥ ግድግዳ ማእዘን ላይ በጭቃ የተሰራ የኩራዝ ማስቀመጫ ይኖራል፤ስሙ ባማርኛ መዝገበቃላትማንበብ ይቀጥሉ…

ህክምናው ይታከም

የዛሬ ሰባት አመት ግድም ጆሮን እያመመኝ በጣም እሰቃይ ነበር፤ጉዳዩን መነሻ አድርጌ” መግባት እና መውጣት” የተሰኘውን ልቦለድ በመፃፍ ፤ስቃዩን ወደ ሳቅ ቀይሬዋለሁ፤ አሁን ያልፃፍኩትን ልንገራችሁ። በድፍን ጦቢያ ዶክተር ነጋን የሚያክል የጆሮ ሀኪም የለም ተባልሁ! ወደ ፒያሳ ወረድሁ፤ ዶክተሩ በትህትና በጨዋነት መረመሩኝ፤ማንበብ ይቀጥሉ…