የብዙኃን እናት…

ሰሞኑን በተወዳጁ ድምጻዊ፣ በጌታቸው ካሳ ላይ የደረሰበትን በሰማሁ ጊዜ አዘንኩ። ጋሽ ጌታቸው በሀዘናችንም፣ በደስታችንም ልናስታውሳቸው የምንችላቸውን ዘፈኖች የተጫወተልን ድምጻዊ ነው። አሁን፣ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የሚሰራበት ቤት በመዘጋቱ ኑሮው እንደተመሰቃቀለ ሲነገር፣ አቤት ይሔ ነገር የስንቱን ቤት አንኳኳ አልኩ። የጌታቸው ካሳ፣ ‹ሀገሬንማንበብ ይቀጥሉ…

ሕዝባዊ ከያኒው

ሕዝባዊ ገጣምያን፣ እነዚያ ሬዲዮ ጣቢያ የሌላቸው፣ ግጥም ማንበብያ መድረክ ያልተዘረጋላቸው፣ ግጥሞቻቸው የሚያሳትሙበት ጋዜጣም ሆነ ሌላ ሚዲያ ያልተመቻቸላቸው እነዚያ አዝማሪያንና አልቃሾች ነገሥታቱን ብቻ ሳይሆን፣ በሕብረተሰቡ ውስጥ ልሂቅና ጉልህ የተባለውን ሁሉ ይተቻሉ። ቃሉን ያጠፈውን፣ በሕዝብ ላይ የቀለደውን ይገስፃሉ። ንጉሥ ሣህለሥላሴ ንጉሥ ፣ማንበብ ይቀጥሉ…

‹አንበሳው› ማን ነው፤ ‹አህያውስ› የምን ምሳሌ?

አንበሳን የማምለክ አባዜ በየጉዳዮቻችን ውስጥ ገንኖ ይታያል፤ የምንወዳቸውና የምንፈራቸው ነገሮች በ‹አንበሳ› ስም እንዲጠሩ እንፈልጋለን፤ የሚያገሱ በሚመስሉ የአንበሳ ሀውልቶች ታጥረን መኖር እንፈልጋለን! በተቃራኒው ደግሞ፤ አህያን እዩት፤ የውርደት ምልክት ነው፤ አንድም ቦታ ጠላቶቹን ድል ስለማድረጉ የሚተርክ ተረት አጋጥሞኝ አላነበብኩም ፤ በተረቱ ውስጥማንበብ ይቀጥሉ…

ጐጆ ቤት

ሀገርስ ጐጆ ናት !!! መሪዋም ምሰሶ ሹማምንቷም ማገር  አንዳንዶቹም ቋሚ ሌሎቹም ወጋግራ ሰራዊቷም አጥር! ሀገርስ ጐጆ ናት !!! ሕዝቡም ክዳን ሆኖ ጐጆውን አልብሶ እንደሳር ቢቀጥን፤ ቢኖር ተራ መስሎ ከዝናብ ያድናል፤ ውርጩን አሰናብቶ ፀሃይን ይከላል፤ በጥላው ከልሎ… ሀገርስ ጐጆ ናት !!!ማንበብ ይቀጥሉ…

በኅዳር ውስጥ እኔን

(የነፍሴ ክስ) ተወው! ቆሻሻህን ተወው  ከሳቱ ዳር እራቅ ጭለማን ልበሰው ጥቁር ካባ ደርብ ዓይንህ ይጨልመው። … ግዴለህም ተወው እቤትህ ግባና ዓይንህን ጨፍነህ ስላሳመምካቸው ስላቆሰልካቸው ነፍሳት አስብና ራስህን ክሰስ ራስህን ውቀስ ራስህን አጥን ተረማመድበት በንፁሀን ፋና። … የነፍስህን እድፍ የውስጥህን ጉድፍማንበብ ይቀጥሉ…

ወንዞች

በሕይወት መንገድ ላይ አሉ ብዙ ወንዞች ምንሻገራቸው  ወንዙ ፈተና ነው ፈተናው ፈተና አሉት እልፍ ጭንቆች። ስንቶች ተሻገሩ፤ ስንቶች ተወሰዱ ስንቶቹ ሰመጡ ይኼ ነው ጥያቄው ይኸው ነው ሚዛኑ ይኸው ነው ልኬቱ ሰው ከተፈጠረ ሙት እስኪባል ድረስ አፈር እስኪገባ አሉት ብዙ ወንዞችማንበብ ይቀጥሉ…

አንዳርጋቸው ጽጌን በጨረፍታ

አንዳርጋቸው ጽጌ ተፈታ፤እሰይ! በኢትዮጵያ ምድር የበቀለ ሳር ቅጠሉ ሁሉ ሲናፍቀው የነበረ ዜና ነበርና የእሱ መፈታት ለፍትህ ለርትዕና ለሀገር ሲቆረቆሩ ለቆዩና መቆርቆር ለሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንና አፍቃሬ ኢትዮጵያውያን መልካም የምስራች ነው። አንዳርጋቸው የማይሰፈር ዋጋ ከፍሏል።አይተናል፤ሰምተናል። የመፈታቱ ዜና በህይወት ላላሉት ተቃዋሚዎቹ/አሳሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ለሞቱትምማንበብ ይቀጥሉ…

አብይ አህመድ (ዶክተር) በ “ፈርዖን” ፊት

ከአንድ ዓመት በፊት፣ ‹እርካብና መንበር› በሚል ርዕስ፣ ‹ዲራአዝ› በሚል ደራሲ ስም የወጣ መጽሐፍ ላይ እንዳነበብነው፣ መሪነት ድንገት ላያችን ላይ የምንጭነው አክሊል፣ ወይም እግረ መንገዳችንን እንደ ዘበት አንስተን የምናጠልቀው ቆብ መሆን የለበትም ።ስንመኘው፣ ስንጠብቀው፣ በትንሹ ስንለማመደው የነበረ፣ ለራሳችን የምናበረክተው፣ የምንፈተንበት፣ እኛንማንበብ ይቀጥሉ…

እኛ፣ሾፌሩና አውቶብሱ

‹ዛጎል› ልቦለድ ውስጥ የምናገኘው ዮናስ የተባለው ገጸ ባሕርይ እንደሚከተለው ያስባል፤ያምናል፤ይናገራልም! ‘በእኛ ፈቃድ አይደለም ነገሮች የሚከወኑት። እግዜራችን ነው ሾፌር። እሱ ነው ፈላጭ ቆራጭ! እሱ ነው የእኛ ሃይል። በየትኛው ጊዜ – በየትኛው ቦታ – እኛን ከመኪናው ማውረድ እንዳለበት የሚወስን። እኛ ‘ወራጅ አለ’ማንበብ ይቀጥሉ…