(ማሳሰቢያ፤ የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ የህክምናም ሆነ የስነ ምግብ ባለሙያ አይደለችም፡፡ በዚህ ፅሁፍ ላይ የተካተተው መረጃ በግል ልምድ ላይ የተመሰረተ እና ለሌሎች ይጠቅም ይሆናል ከሚል ቀና አስተሳሰብ የመነጨ ምክር እንጂ በጥልቅ መረጃና ሳይንሳዊ መሰረት ላይ የቆመ ነው ለማለት አይቻልም) ከተወለድኩ አንስቶማንበብ ይቀጥሉ…
ታማሚና ጠያቂ
ትወለጃለሽ፤ትኖርያለሽ፤ትሞቻለሽ፤ በየጣልቃው ግን ትታመምያለሽ! ሳይንሳዊ ሀቅ ነው!! በሽታ ድሮ ቀረ! ደሞ የዛሬ ልጅ ምን በሽታ ያውቃል? የኔ ትውልድ መኩራት ሲያንሰው ፤ እነ ፈንጣጣን፤ እነ ፖሊዮን፤ እነ ትክትክን፤ እነ አባ ሰንጋን ሸውዶ ነው እዚህ የደረሰው፤ በሽታ ብቻ ሳይሆን በሽተኛ ራሱ ድሮማንበብ ይቀጥሉ…
ኤልያስ፡- ሀገር ነው እኖርበታለው!
የጌቴ አንለይ፥ የቀይ ጥቁር ጠይም፣ የቤሪ፥ ሕሊና እና የልዑል ኃይሉ፥ አንቺ ነሽ አካሌ ዘፈኖች በቁጥር ሶስት ቢሆኑም፥ በመንፈስ አንድ ናቸው። ከኢትዮጵያዊው ኤልያስ ማህፀን የተማጡ። ወንዱ ኤልያስ ወላድ ነው፥ ያውም ልበ መልካሞችን የሚወልድ። እያንዳንዳቸው ዘፈኖች ብቻቸው ቁመው መነበብ ቢችሉም፥ ሶስቱም ገምደንማንበብ ይቀጥሉ…
ሲስተርሊ ብራዘርሊ – (ክፍል ሶስት)
እንዲህ ስድ መሆኔን፣ ኬቢ ላይ እንዲህ መባለግ መቻሌን ማመን አቃተኝ። ግን ይሄ ግልብ መልስ ከልክ በላይ አንድዶት፣ ይሄንን ድብብቆሽ ቶሎ የሚያፈርስና ‹‹እወድሻለሁ›› የሚያስብለኝ፣ ለአመታት የጠበቅኩትን ልጅ በደቂቃዎች የሚሸልመኝ ስለመሰለኝ እንደዚያ አልኩ። ልቡ በተሰበረ ሰው አኳሃን አየኝ። እመኑኝ፤ አግኝቼዋለሁ። በድንገት ቀናማንበብ ይቀጥሉ…
ሲስተርሊ-ብራዘርሊ (ክፍል ሁለት)
ህእ….ልወደው ነው እንዴ? አዬ..በምን እድሌ? አይደለም። እስካሁን ያወራሁላችሁ ሁሉ ስለ ኤፍሬም አይኔ ያየውን፣ አንጎሌ የመዘገበውን እንጂ አብላልቼ፣ ሳላስበው ለልቤ የነገርኩት፣ ልቤም ከእኔ የተቀበለውን የውደጂው ጥሪ ተቀብሎ ንዝንዙን የጀመረበት…ልክ ኬቢን የወደድኩበት መንገድ የሚመስል አይደለም። (አያችሁ….አይንና አንጎል ገለልተኞች ናቸው። ሊስት ይዘው ሰውማንበብ ይቀጥሉ…
‹‹ሲስተርሊ- ብራዘርሊ››
ከዶ/ር መረራ ኢንትሮዳክሽን ቱ አፍሪካን ፖሊቲካል ሲስተምስ ክላስ ስንወጣ ‹‹ ዛሬ ተሳክቶልኝ ኤፊን ላስተዋውቅሽ ነው›› አለኝ ክብሮም። ክብሮም፣ በእሱ ቤት ‹‹ንፁህ›› ጓደኛዬ ነው። (በነገራችን ላይ…ንፁህ ጓደኛ ሲባል ያስቀኛል። ወንድና ሴት ‹‹እሱ እኮ ንፁህ ጓደኛዬ ነው…እሷ እኮ ንፁህ ጓደኛዬ ናት›› የሚባባሉትማንበብ ይቀጥሉ…
‹‹ለፀጥታ እንከፍላለን››
ከበር እንደገባሁ፣ ልክ እድሜ ልክ ሳደንቀው እንደኖርኩ ታዋቂ ሰው ሳየው ተንሰፍፌ አብሬው ‹‹ሰልፊ›› የተነሳሁት ከሰፋፊ ቅጠሎች ጋር ነው። እነዚህ ቅጠሎች በልጅነታችን ከደጃፋችን እንደዋዛ ቀጠፍ አድርገን ለጢባጢቢ የምንጠቀምባቸው ነበሩ። እዚያ ጋር እንደ ብርቅ መአድን የምነካካው ዛፍ ልጆች ሳለን ከሰው ግቢ ገብተንማንበብ ይቀጥሉ…
ሞቱ በስርአት
ጥሩንባ ተነፋ ህልፈት ተለፈፈ እድር ቢያሰማራው ፤ህዝቤ ተሰለፈ የቅፅር ጥድ መስሎ፤ የተከረከመ በስልት እየሄደ፤በወግ እየቆመ ፖሊስ ከነ ማርሹ፤ ቄሱ ከነፅናው ፤ ከሳሹ ወራሹ፤ ወዲህ አሰለቃሹ፤ወዲህ የሚያፅናናው፤ ሁሉም ባጀብ ያልፋል፤በፈሊጥ፤በፊናው፤ ከቀብር መልስ ግን፤የንቧይ ቤት ሆነና፤ ተቀልሷል ሲባል፤ተመልሶ መና መንገድ ላይ ሲጋፋማንበብ ይቀጥሉ…
‹‹ሃገሬ ቆማበት››
ቢሮ መግቢያዬ አካባቢ ዘወትር ማለዳ አላጣውም። አንድ እግር የለውም። ሆኖም ሁሌም ክራንቹን ተደግፎ በፍጥነት ወዲህ ወዲያ ይላል። ሁለት የባለፀጋ ልጆች የሚማሩባቸው ትምህርት ቤቶች ደጃፍ ነው ላይ ታች ሲል የሚያረፍደው። ልጆቻቸው ከመኪና ወርደው ሶስት አራት እርምጃ በእግራቸው ቢራመዱ እንደ እንቁላል ከሽ፣ማንበብ ይቀጥሉ…
ውጉዝ ከ መ ቄስ በላይ
በድሮ ዘመን አንድ አርዮስ የሚባል የነገረ ክርስትና ሊቅ ነበረ። እነሱ “አርኪሜዴት“ የሚሏቸው ስብስብ ደረጃ የደረሰ ሁላ ነበር። እናም በዛን ዘመን ጋሽ አርዮስ ተመራመርኩ፡ አወኩ አለና(በሴይጣን አነሳሽነትም ይመስለኛል) ቤተክርስትያንን ለሁለት የሚከፍል የኑፋቄ ትምህርት ይዞ ተነሳ። በዚህ ዘመን ደግሞ ቄስ በላይ የሚባልማንበብ ይቀጥሉ…