የታሪክ ሃሳብ፡ ዶርቲ ፓርከር ‹‹The Sexes› (1926) አኩርፌዋለሁ። ሳሎኔ እንደገባ ‹‹ተቀመጥ›› ብለውም ሶፋዬ ላይ አኩርፌ በተቀመጥኩበት ቁልቁል ያየኛል።ፈራ ተባ ይላል፣ አይኑ አይኔን ይሸሻል። ከገባ ከሁለት ቃል በላይ ደፍሮ ማውጣት ተስኖታል። ፈርቶኛል። ይሄንን ታላቅ የኩርፊያ ደመና በምን እንደሚበትነው ስለጨነቀው ፈርቶኛል። የልብማንበብ ይቀጥሉ…
የማብራትና ማጥፋት ወግ
(የመጨረሻው ክፍል) ባገራችን፤ በባላባት ስርአት ወግ “ፈናወጊ “ የተባሉ አገልጋዮች ነበሩ፤የስራ ድርሻቸው ፋኖስ፤ አንዳንዴም ጡዋፍ ይዞ መቆም ነበር፤ራት ላይ ከጌቶች እና ከእመቤቶች ማእድ ትንሽ ፈንጠር ብለው ቆመው ያበራሉ፤ በቤተመንግስት ውስጥ መብራት ተሸክመው የሚያነጉም ነበሩ፤የመጀመሪያዎቹ የመብራት ምስሶዎች ነበሩ ማለት ይቻላል፤ ታድያማንበብ ይቀጥሉ…
‹‹አፍሪካዊነት በጎነት››
እዚህ ኮንዶሞኒየማችን አራተኛ ፎቅ ላይ አንዲት ቆንጆ ልጅ አለች….ቁንጅናን ሳይሰስት የሰጣት እሷም ሳትሰስት ውበቷንና ሽቶዋን ለብሎኩ ነዋሪዎች በቸርነት የምታሳይ ቆንጆ ! እውነቴን ነው …አንዴ ስታልፍ ከአንደኛ ፎቅ እስከአራተኛ ፎቅ ደረጃው ሁሉ የሷን ውድ ሽቶ ይታጠንና ባለአራት ፎቅ ገነት ይመስላል ….በአካልማንበብ ይቀጥሉ…
የየመኒዎች ጨዋታ
በዚህ ወቅት የቅርብ ጓደኛዬ የመኒው ኮሎኔል ሙሐመድ አል ሐይደሪ ነው። ረመዳንን በአብዛኛው አንድ ቤት ነበር ያሳለፍነው። አሁንም አብረን ነው የምንውለው። በተለይ ከሰዓት አብረን ስንጫወት ነው የምናሳልፈው። በርካታ ቁም ነገሮችንም ከእርሱ እየተማርኩ ነው። —- ጦርነትን ሸሽቶ ከሀገሩ የወጣው ሙሐመድ አል ሐይደሪማንበብ ይቀጥሉ…
ሲጨልም
የመብራት የመጥፋት ትዝታ፤ከባለፈው የቀጠለ
ከጥቂት አመት በፊት የረር በር እኖር ነበር፤አንድ ቀን መብራት በጊዜ ጠፋ፤እስከ እኩሌሊት ድረስ ስላልመጣ ተስፋቆርጠን ተኛን፤ ዘጠኝ ሰአት ላይ ሚስቴ ቀሰቀሰችኝና ወደ ምኝታቤቱ መስኮት ጠቆመችኝ፤ የሆነ ግዙፍ እጅ ጥላ መስኮቱን ሲዳብስ ይታየኛል፤ “ሌባ ነው?” አልኩዋት፤ ራሱዋን ባዎንታ ወዘወዘች፤ “መስኮቱን ምንማንበብ ይቀጥሉ…
እምዬ ያልታደለች
እምዬ ያልታደለች ተመዘኚ ሲሏት— መዛኝ ነኝ ትላለች እምዬ ሰከረች ልትመዘን ወጥታ — መዛኝ ሆና ቀረች! የቅቤን ስብራት — በቅመም ለማከም በወቀጣ መዛል — በድለዛ መድከም የቅቤን ወለምታ — በቅመም ለማሸት ሲደቁሱ አድረው — ሲቀይጡ ማምሸት የቅቤን ጉብዝና — በቅመም ለማትጋትማንበብ ይቀጥሉ…
ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ባለስልጣን ጋር በመተባበር የተቀሰቀሰ ትዝታ
ወደዚች ምድር ስመጣ ማንኩሳ በጭላጭ ኩራዝ ተቀበለችኝ፤ ኩራዙ ያራት ነገሮች ጥምረት ነው፤ የኮኮስ ቅባት ጠርሙስ፤ በምስማር ተበሳ ቆርኪ፤ የዝሃ ክር እና ላምባ። በጊዜው የኩራዝ ማብሪያ መቅረዝ አይታወቅም፤ ከያንዳንዱ ጎጆ የውስጥ ግድግዳ ማእዘን ላይ በጭቃ የተሰራ የኩራዝ ማስቀመጫ ይኖራል፤ስሙ ባማርኛ መዝገበቃላትማንበብ ይቀጥሉ…
ሞቶ ያልቀበርነው ፊልማችን!
እንዴት አደራችሁ ጎበዛዝት? እኔ አላሁ አክበር ሳይል ከእንቅልፌ ነቅቼ እስኪነጋ ድረስ ዩቲዩብ ላይ የተለቀቀ የአማርኛ ፊልም ከፈትኩ። ጎበዝ! እኛ ኢትዮጵያውያን የፊልም ነገር ምንም አልተዋጣልንም። የፊልሙ ኢንደስትሪያችን (ኢንደስትሪ ከተባለ) ከቀን ወደቀን ተስፋ አስቆራጭ እየሆነ ነው። ድርሰቱ፣ ፕሮዳክሽኑ ምናምን ምንለው አይደለም ባጭሩማንበብ ይቀጥሉ…
ትንንሽ ቅመሞች
ቅዳሜ ቅዳሜ ማታ በዙረቴ የማልደርስበት የከተማችን ክፍል የለም። ሳምንት ወይ አስራ አምስት ቀን በሙሉ ከቤት ሳልወጣ እቆይና፣ እመሽግና አንድ ቅዳሜ መርጬ ከወጣሁ ግን የምመለሰው ተበለሻሽቼ ነው። በደንቤ ሳምንት፣ ሁለት ሳምንት ሙሉ ከቤት አልወጣም…… ከእሁድ እስከ ዓርብ። ብዙ ጊዜ ቅዳሜ ግንማንበብ ይቀጥሉ…