ጉደኛ ስንኞች

እንዳለመታደል ሁኖ የጎጃሙ ጌታ የራስ አዳል ልጆች አሪፍ ያገር አስተዳዳሪ አልነበሩም። እንደመታደል ሆኖ ደሞ የተዋጣላቸው ባለቅኔዎች ነበሩ። ግጥሞቻቸው ከኑሯችን ጋር በጣም የተቆራኙ ናቸው። ለምሳሌ የግፍ ዘገባ በሰማን ቁጥር የምንቀባበለው። “የለህም እንዳልል ይመሻል ይነጋል አለህም እንዳልል እንዲህ ይደረጋል” የሚለውን ገራሚ ግጥምማንበብ ይቀጥሉ…

ኖረሽ እይው በቃ

(ለoptimistቶች) ጨለማ ነህ ብለሽ እኔን ስትተቺ ዘልለሽ አትጠግቢ ስቀሽ አትሰለቺ ወርሃ- ፅጌ ነው አመት ሙሉ ላንቺ። ደሞ በየቀኑ ፋሲካ ነው ኑሮሽ ያለም ሰቀቀኑ ሩቅ ነው ለጆሮሽ (የፍጥረት ሰቆቃ) ለጋ ነው አእምሮሽ ገላሽም ነው ጮርቃ ሌላም አልልሽም ኖረሽ እይው በቃ። በየጎዳናሽማንበብ ይቀጥሉ…

ካልፎሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ

ባለፈው ከውጭ ወዳገር ቤት ስመጣ አንዱ ደውሎ:- ” ጀለስካ ወዳገር ቤት ለመግባት ኤርፖርት ታይተሃል የሚባል ነገር ሰማሁ ልበል” ” ልክ ነው!” “በሩ ላይ ጠብቀኝ ታክሲ ይዤ መጣሁ” “እቃ ውሰድልኝ ልትለኝ ባልሆነ?” “ምናለበት ብትቸገርልኝ” ” አዝናለሁ ሻንጣየ ውስጥ ላየር ማስገብያ የሚሆንማንበብ ይቀጥሉ…

እኔ እምፈልገው

እውነት ለመናገር፥እኔ እምፈልገው ካንቺ ጋር መጋባት ይህን ሐምሌ ፊቴን፥ ደጋግሞ ማራባት ከወፎች ጋር መንቃት፥ በጊዜ ቤት መግባት “ምንም ድሀ ቢሆን፥ ባይኖረውም ሀብት ከደጃፍ ሲቀመጥ፥ ደስ ይላል አባት” ለሚል መናኛ ጥቅስ ፥ ኑሮየን ማይመጥን ሲሻኝ በየባንኩ፥ ስፈልግ በሳጥን የተረፈኝ ገንዘብ ደጃፍማንበብ ይቀጥሉ…

ድንኩዋን ሰባሪው

  አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ከድህነት ወለል በታች የሚኖር ነው። የቸሬ ድህነት ግን ወለል እንኩዋ የለውም። ከቸሬ ጋር ስትወዳደር ድህነት ራሷ ሀብታም ናት። እኔ ግን ምናለ መፈላሰፉን ትቼ ወደ ታሪኩ ብገባ ! በቀደምለት ቸሬ ተፈናቃይ ወገኖቻችንን በጉልበትና በፀሎት ለማገዝ ወደ ስፍራውማንበብ ይቀጥሉ…

ወፋ በፌስቡክ

በድሮ ጊዜ በኢትዮጵያ ባንዳንድ ገጠሮች ውስጥ “ወፋ” የሚባል ልማድ ነበር። ያንድ ቀበሌ ባላገሮች ከወንዝ ወዲህ ማዶ እና ወድያ ማዶ ተሰላልፈው በጩቤ በጦር በዱላ ይከሳከሳሉ። አንድ ባላገር ከገበያ ሲመለስ የወፋ ጦርነት ሲካሄድ ከተመለከተ ቆም ብሎ ቅርጫቱን ያስቀምጣል። ከዚያ በቅርብ ከሚያገኘው ጎራማንበብ ይቀጥሉ…

ቅንጣቢ የምፅዋ ወግ

‹‹የት ነው የሚሄደው? ›› ይሉኛል መአት ሰዎች እየተፈራረቁ። በትግርኛ ነው የሚጠይቁኝ። በግምት ነው የምመለሰው። ከንጋቱ 11.45 ላይ አስመራ አውቶብስ ተራ ላይ ያረጀ ኮሰተር አውቶብስ ውስጥ ብቻዬን ተቀምጬ ሲያገኙኝ ሌላ ምን ሊጠይቁኝ ይችላሉ? ከአዲስ አበባ አውቶቢስ ተራ ጋር ሲነፃፀር በውክቢያም በስፋትምማንበብ ይቀጥሉ…

ቅንጥብጣቢ የአስመራ እና የምፅዋ ወግ (ክፍል ሶስት)

አስመራ – ከተወራላት በላይ የምታምረው ከተማ አዲስ አበባ እና አስመራ በብዙ ነገር የተለያዩ ከተሞች ይሁኑ እንጂ በተለይ የድሮዋን አዲስን ለሚያውቅ ሰው የአስመራን መልክ መገመት የሚከብድ አይመስለኝም። እስቲ ድፍን ፒያሳን አስቡ። ብሄራዊ ቲያትር አካባቢን፣ አምባሳደር፣ ኢትዮጵያ ሆቴል አካባቢን ጨምሩ። ሜክሲኮ የድሮውንማንበብ ይቀጥሉ…

ቅንጥብጣቢ የአስመራ እና ምፅዋ ወግ (ክፍል ሁለት)

አስመራ- ከተወራላት በላይ የምታምረው ከተማ ለስድስት ቀን ቆይታዬ በፊልሞን አማካኝነት ወደተያዘልኝ አምባሳደር ሆቴል ገባሁ። የእንግዳ መቀበያውና በኋላ ያየሁት በስተግራ ያለው ሻይ ቤት ነገረ ስራው ሁሉ የፒያሳውን ቶሞካ አስታወሰኝ። ሞቅ ባለ ሁኔታ የተቀበለኝ አስተናባሪ ሻንጣዬን ይዞ ክፍሌን የሚያሳየኝ ጎልማሳ መድቦልኝ አሳንሰሩማንበብ ይቀጥሉ…

ቅንጥብጣቢ የአስመራ እና ምፅዋ ወግ

አስመራ- ከተወራላት በላይ የምታምረው ከተማ ‹‹እናት ብዙ ሻንጣ የለሽም አይደል? እባክሽ ይህቺን ስኳር ያዢልኝ? የእኔ እህት….ኪሎ በዝቶብን ነው…ይህችን ቡና ትይዥልኛለሽ?….እመቤት… ያንቺ አልሞላም አይደል…እባክሽ እነዚህን ጫማዎች ያዢልን…›› እያሉ ብዙ ሰዎች ያዋክቡኛል። ቦሌ አየር ማረፊያ አስመራ የሚወስደኝን አውሮፕላን ለመሳፈር ሻንጣ ማስረከቢያው ጋርማንበብ ይቀጥሉ…