“ያ’ባ ምናሴ ፍትህ”

በአንዲት “ሊቃውንት” በሚበዙባት ደብር ውስጥ የኒህ የሁለቱ ሊቃውንት ፀብ ለያዥ ለገናዥ አስቸጋሪ ሆነ። በቃላት ምልልስ የጀመረው የመሪጌታ ቀፀላ ኤፍሬም እና የቀኝጌታ በፍርዱ ሄኖክ ፀብ፤ እጅጉን ብሶበት በምዕመናኑ ፊት ከዓውደ ምህረቱ ስር ለድብድብ ተጋበዙ። በቅርብ የተገኙት፤ ከቅዳሴ የወጡት ቆራቢ ምዕመናን ገላግለው፤ማንበብ ይቀጥሉ…

አዲሳበባ የማን ናት?

ወገን ይቅር በለኝ!! እርሱን የመረጥኩት ስለ ስነፅሁፍ ግድ የማይሰጣቸውን ፊስቡከኞች ትኩረት ለመሳብ ብየ ነው። ርእሱ ሲተረጎም may I have your attention ? እንደ ማለት ነው። ከታች ያለው ወግ ስለ አዲሳበባ አይደለም። ስለ አዲሱ የግጥም መፃፌ ነው። እስቲ በስምአብ ብየ ማካበድማንበብ ይቀጥሉ…

ስለ ፍቅር ሲባል!

<በዘመኑ በመፈጠሬ እኮራለሁ> ብል ታበይክ እሚለኝ እሱ ማነው?ፍቅር እና ትዕቢት ባንድ መንበር አብረው እንዳይቆሙ እናውቃለንና። ዳሩ ግን ሰውየው በፊደል ቆጠራ የልጅነት ዘመኔ አቡጊዳ ብሎ በዜማ ሀሁ እንደለከፈኝ አለ።ነፍስ ባላወቀ ቦላሌ ባላንጠለጠለ የልጅነት ዘመናችን ነፍሷ በሰማይ ካለ አብሮ አደጌ ካዲሴ እናማንበብ ይቀጥሉ…

መማርና መማር

(ሲጠብቅና ሲላላ) ትዳርን የተቃናና የተሳካ ለማድረግ በሁለት ባላዎች ላይ መትከል ያሻል ይላሉ ሊቃውንቱ። በመማርና በመማር። ሰው ሌላውን ሥራ ሁሉ የሚሠራው አንድም ተምሮ አንድም ለምዶ ነው። ትዳር ሲመሠርት ግን ትምህርትም ልምድም የለም። ትዳርን እንደ ትምህርት ዓይነት መርጦ፣ ከፊደል እስከ ዳዊት ደግሞ፤ማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹እድሜ ለግንቦት ሃያ…››

በግንቦት 20 ዋዜማ ዋልታ ቴሌቪዥንን እያየሁ ነው። ጋዜጠኛው ዝግጅቱን ከአመት አመት በማይቀየሩት መፈክሮች( ለምሳሌ “ግንቦት 20 የህዝቦች ሁሉ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ ያገኘበት ቀን ነው) ጀመረና፣ ዛሬም በጭንቅላቴ ውስጥ የሚፈነጩትን ጥያቄዎች ዘርዝሬ ለማሰብ እንኳን እድል ሳይሰጠኝ፣ “ከግንቦት 20 ወዲህ የተወለዱ ልጆችማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹ገዳዬ…ገዳዬ…››

(መነሻ ሃሳብ፤ የሞፋሳ (ኬንያዊ ገጣሚ) ‹‹ልጅቷ›› ግጥም) ፀሐያቸው ጠልቃ በሰው ሀገር መሽቶብኝ ነበር። ጨልሟል። የተለመደውን አውቶብሴን ተሳፈርኩ። አዲስ ነገር የለውም። ሁሌም የምጠብቀው፣ ሁሌም በጠበቅኩት ሰአት የሚመጣው የማይዛነፍ የእለት ውሎዬን የሚደመድመው አውቶብስ ነው። እንደተቀመጥኩ፣ ሰንደቅ የሚያሰቅል ቁመት ያለው ውብም፣ ሎጋም ኢትዮጵያዊማንበብ ይቀጥሉ…

እንግዶቹ

“… ዓይን ወረተኛ ነው ያመጣል እንግዳ’’ የሚል ስንኝ ያለበት የባላገር ዘፈን አውቃለሁ፤ በርግጥ ዘፈኑ እንደሚነግረን ዓይን ብቻ አይደለም አዲስ ለምዶ እንግዳ ይዞ የሚመጣው፤ ጆሮም፣ ልብም፣ እጅም፣ እግርም መጠናቸው ይለያይ እንደሆነ ነው እንጂ፣ ከአዲስ ነገር ጋር አስተዋውቀውንና አላምደውን እንግዳ ይዘውብን ይመጣሉ።ማንበብ ይቀጥሉ…

ካልፎ ሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ

(ትራጄዲ ትረካ) ሰሞኑን የወንድሙ ጂራን ዘፈን የምገርበው ያለ ምክንያት አይደለም። ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ ካልሲየን ፍለጋ በየጥጉ እሰማራለሁ። የቀኝ ካልሲየ ምስኪን ናት። እንደ ገራም የድመት ግልገል ከመመገቢያው ጠረጴዛ እግር ስር ኩርትም ብላ ትገኛለች። የግራ ካልሲየን ግን እፀ -መሰውር የረገጥሁባት ይመስል ደብዛዋማንበብ ይቀጥሉ…

ጋሹ እንዴት እንደተሰደደ?

  የዚች ጨዋታ መነሻ የሆነኝ የዛሬ ምናምን አመት ያነብኩት “ያረብ ሌሊቶች ” ተረት ነው። ጋሹ ታታሪና አይናፋር ባላገር ነው። ሲኖር ሲኖር; በስንት መከራ አንዲት ቆንጆ አጭቶ አገባ። የሰርጉ ቀን ተበልቶ ተጠጥቶ ጭፈራው ደራ። ሚዜዎችና አጃቢዎች ሙሽሮች እንዲጨፍሩ ጋበዙዋቸው። ጋሹ ግብዣውንማንበብ ይቀጥሉ…

ኢትዮጵያ በአማልክት እና በተከታዮቻቸው ዓይን

“… እናቴ ሆይ በዚህች በምባርካት አገር በኢትዮጵያ የሚኖሩ ሰዎችን እስከ ዓለም መጨረሻ ድረስ አሥራት ይሆኑሽ ዘንድ ሰጥቼሻለሁ። እናቴ ሆይ አሁንም ወደዚያች አገር እንሄድ ዘንድ ተነሺ። ደሴቶችና የተቀደሱ፣ ወንዞችዋ ያማሩ፣ ውሃዎችዋ የጠሩ፣ ዛፎችዋና ተራራዎችዋ የተዋቡ ናቸውና አሳይሻለሁ አለኝ።” ይላል አንብር መስቀልየማንበብ ይቀጥሉ…