ራይድ ለመዲናይቱ አሪፍ ጸጋ ነው ፤ ለብዙ ሰው ስራ ፈጥሮ የብዙ መንገደኞችን ኑሮ አቅልሏል፥ ራይድ የሚሰሩ ሰዎች መካከል አንዳንዶቹ እንደኔ የክፍለሀገር ልጆች መሆናቸውን መርሳት አይገባም፥ ባለፈው አንዱ ባለ ቢትስ መጣልኝ፥ ጢንጥየ መኪና ናት፤ አራት ጎማ ያላት የዲዮጋን ቀፎ በላት፤( አሁንማንበብ ይቀጥሉ…
“መዶሻህን ብላው”
ወዳጄ (Netsanet) እንደነገረኝ ሰውዬው እሁድ ቀን እቤቱ ጋደም ብድግ ሲል ይቆይና ግድግዳው ላይ የተነቀለች ሚስማር አይቶ ሊመታት ቢፈልግ መዶሻ ያጣል። ጎረቤቱን ሊጠይቀው በሩጋ ከደረሰ በኋላ «ተኝቶ ቢሆንስ» ብሎ ይመለሳል። እቤቱ ከመድረሱ በፊት ግን «እህ የተኛ እንደሆነስ? መዶሻውን ከሰጠኝ በኋላ ተመልሶማንበብ ይቀጥሉ…
የጥልቁ ትንታኔ
በቀደም ስለሉሲፈር ፊልም በፃፍኩት ፅሁፍ ስር አንዱ “ትውልዱን በማር የተለወሰ መርዝ እያስነበብሽው ነው” ብሎኝ ሳቅቼ ሞተውት። እናውራ እንዴ? የትኛውን ትውልድ? ይሄ ትውልድ ቲክ ያላደረገው የሉሲፈር ስራ አለ ነው የምትሉኝ? ይሄ የኔ ዘር አይደለህም ብሎ ወንድሙን ዘቅዝቆ የሚሰቅለው ትውልድ ሉሲፈር እሩቁማንበብ ይቀጥሉ…
ካንደኛው ፌርማታ ወዳንዱ ስሻገር
ይፈርስ የማይመስል፥ እስከ ዘላለሙ አምና እዚህ ቦታ ላይ ፥አንድ ሱቅ ነበረ የሱቁ ባለቤት ሚፍታህ ነበር ስሙ፤ ሙሉቀን ሲተጋ፥ በከፊል የሚታይ፥ እንደዜና አንባቢ፥ በሱቁ መስኮት ላይ ከወገቡ በላይ፥እየተገለጠ ለወጭ ወራጂው፥ ፈገግታ እየሰጠ ሸቀጥ እየሸጠ በጋዜጣ ቅዳጅ እየጠቀለለ በልቃቂት አምሳል እየሸበለለ “የሁለትማንበብ ይቀጥሉ…
“lucifer”
በራሴ ጉዳይ ተንበርክኬ የፀለይኩበት ቀን በጣም እሩቅ ነው። እውነት ለማውራት ከጠየቅኩት በላይ የማይገባኝ ሁላ የተሰጠኝ ሰው ነኝና ብዙም ጥያቄ የለኝም! ከፍቶኝ ፊቱ የቀረብኩባቸውንም ቀናት formal ፀሎት የፀለይኩባቸው ቀናት በጣም ድሮ ናቸው። አጠገቤ ሆኖ እንደሚሰማኝ እነጫነጫለሁ። «ከዚህ በላይ መሸከም እንደማልችል አታውቅም?ማንበብ ይቀጥሉ…
ሚሽኑ
አሳዛኝ ታሪክ ትናንት በራፌ ተቆረቆረ፤ ከፈትኩ፥ ሁለት ያሜሪካ ወታደራዊ መለዮ የለበሱ ሰዎች ቆመዋል ፤ ባለባበሳቸው መገመት እንደቻልኩት አንደኛው ፊልድ ማርሻል ነው፤ ሁለተኛው ፊልድ ሻለቃ ሳይሆን አይቀርም፥ “ሚስተር ቤኪቱ” ብሎ ጠራኝ ማርሻሉ ፥ “አቤት” “እንኳን ደስ ያለህ ለብሄራዊ ውትድርና አልፈሀል! “ማንበብ ይቀጥሉ…
የባላንታይን ዋዜማ ወግ
ከብዙ ዘመናት በሁዋላ ከወዳጄ ምእዝ ጋራ ትናንት በስልክ ተገናኘን፤ ላንድ ሰአት ተኩል ያክል ስናወጋ የተረዳሁት ነገር ፤ጊዜ ብዙ እንዳልቀየረን ነው፤ “የት ልትጋብዛት ነው ያሰብከው?” ሲል ጠየቀኝ፥ “ራቅ ያለ ሰፈር ልወስዳት ነው ያሰበኩት፤ እኛ ሰፈር ያሉት ሬስቶራንቶች ሁሉ ያውቁኛል” “በሬስቶራንቶች ውስጥማንበብ ይቀጥሉ…
የሰንበት ትዝታዎች
ለመጀመርያ ጊዜ ሲኒማ የገባሁት አስራንደኛ ክፍል ሳለሁ ይመስለኛል፤ እሁድ ቀን ደብረማርቆስ ውስጥ ነው፤ ብቸኛው ሲኒማ ቤት ተከፍቶ ካስራምስት የማንበልጥ ሰዎች ታድመናል፤ ፊልሙን በቴክኒክ የሚቆጣጠረው ሰውየ የጤና እህል ማለቴ እክል ገጥሞት አልመጣም፤ ስለዚህ፥ የሲኒማ ቤቱ ዘበኛ ጋሽ ይትባረክ ሰውየውን ተክተው ለመስራትማንበብ ይቀጥሉ…
ተቆርጦ የቀረው
በየነ ባልንጀራየ ነው፤ ጦርነቱ ሲጀመር “በዩማ ቲዩብ “ የሚል የዩቲዩብ አካውንት ከፍቶ መሸቀል ጀመረ፤ አንዳንዴ የድል ዜና ሲጠርርበት ሰለ አድዋ ወይም ስለዶጋሊ ድል በመተረክ ፕሮግራሙን ይሞላዋል፤ አንዳንዴ የኔን ግጥም ሳይቀር ከፌስቡኬ ላይ ወስዶ ይዶልበታል፤ ሳንቲም ማካፈሉ ይቅር ፤ ክሬዲት እንኳማንበብ ይቀጥሉ…
‹‹ብንሄድ ብንሄድ- አንደርስም ገና ነው››
ቴዲ አፍሮ ‹‹ቀና በል›› የሚለውን ሙዚቃውን በለቀቀ ማግስት ለስራ ጉዳይ ጎረቤት ሃገር ተላክሁ። ከአየር ማረፊያው ወደ ሆቴሌ የሚወስደኝ ታክሲ ውስጥ ገብቼ ብዙዎችን ያላቀሰውን ሙዚቃ በጥሞና ለማዳመጥ የጆሮ ማዳመጫዬን ከስልኬ አገናኘሁ። ልክ ቴዲ ‹‹አርማሽ ይውለብለብ ከደጄ-ልቤ ናፍቆሻል ወዳጄ›› ብሎ መዝፈን ሲጀመርማንበብ ይቀጥሉ…