ደስታን በብልቃጥ

‹‹ላግባሽ›› ብሎ ሲጠይቀኝ… አይኖቼ እንደ ስልሳ ሻማ አምፖል እየተንቦገቦጉ፣ የሰራ አከላቴ እየፋመ፣ ከንፈሬ መርበትበቴን ለማሳበቅ እየተንቀጠቀጠ፣ ሰውነቴ ያለ አግባብ እየተናወጠ… ይሄ ሁሉ አይሰሙ ደስታ እየተሰማኝ ፤ ቃላቶቼን መጥኜ፣ መፈንደቄን ደብቄ ቀዝቀዝ አልኩና፣ ረጋ አልኩና፣ በሴት ልጅ ወግ፤ ‹‹እሺ…›› አልኩት። ይወደኝማንበብ ይቀጥሉ…

የጓዳ ውስጥ ባሪያ እና የመስክ ላይ ባሪያ

(ይህ ፅሁፍ ከመጠነኛ ጭማሪ እና ቅናሽ በስተቀር ታዋቂው የጥቁር አሜሪካዊያን መብት ተሟጋች ማልኮም ኤክስ በአንድ ወቅት ያደረገው ንግግር ትርጉም ነው ሊባል ይችላል) ማልኮም ኤክስ በሰላሳ ዘጠኝ አመቱ በሰው እጅ ተገድሎ ከሞተ ሃምሳ አንድ አመታት አልፈዋል። በዚህ ንግግሩ ውስጥ ያለው ምሳሌማንበብ ይቀጥሉ…

የሞተን ፈረስ ጥቅም ላይ ስለ ማዋል

ሰሞኑን የምር የሚያሰለጥን ስልጠና ውስጥ ነበር የከረምኩት። ከትምህርቶቻችን አንዱ ፤ ‹‹የሙት ፈረስ አስተዳደር›› በሚል ርእስ የተቀመጠ ነበር። አስደማሚው አሰልጣኛችን ይህንን ትምህርት የጀመረው የሚከተለውን በመጠየቅ ነበር። ‹‹ፈረስ እየጋለባችሁ ነው እንበል። በፍጥነት እየጋለባችሁ ሳለ ፣ ፈረሱ ላይ እንዳላችሁ የፈረሱን መሞት ተረዳችሁ። በዚያችማንበብ ይቀጥሉ…

የቤት እመቤት በመሆን ውስጥ እመቤትነት አለ?

ላለፉት ጥቂት ቀናት ያገኘኋቸውን ወንዶች በሙሉ አንድ ጥያቄ ስጠይቅ ነበር፡፡ ‹‹የቤት እመቤት ምን ማለት ነው?›› ከአንድ ወይም ሁለት መልሶች ውጪ የተሰጡኝ ፍቺዎች በሚከተሉት ሀረጎች ሊጠቃለል ይችላል፡፡ ‹‹የማትሰራ ሴት›› ‹‹ስራ የሌላት ሴት›› ‹‹ገቢ የሌላት ሴት›› ‹‹ስራ አጥ ሴት›› ‹‹ስራ ፈት ሴት››ማንበብ ይቀጥሉ…

ሥልጣኔ የኋልዮሽ

ቀደም ባለው ዘመን ደመቅ ብለው የጠቆሩ የዳር አገር ብሄረሰቦችን በባርነት መፈንገል የተለመደ ነበር። ብዙዎቹ የኦሮሞ የአማራና የትግራይ ጌቶች እልል ያሉ የባርያ ፈንጋይና አሳዳሪ ነበሩ።ተፈንጋዮቹን ለፍንገላ ያጋለጣቸው ከነሠንሠለታቸው ስለተወለዱ አልነበረም። ማስገበር ደንብ በነበረበት በዚያ ዘመን ራሳቸውን የሚመክቱበት ነፍጥ ወይም አደረጃጃት ስላልነበራቸውማንበብ ይቀጥሉ…

ያድዋ ስንኞች

የቅዱስ ቫላንታይንን በአል ምክንያት በማድረግ ስለ አድዋ ጦርነት እንጽፋለን፡፡ የቀድሞ ሰዎች የቃልና የዜማን ኃይል አሳምረው ያውቃሉ፡፡ ስለዚህ ሁሌም ወደ ጦርሜዳ ከመሄዳቸው በፊት አዝማሪ እና አረሆ ይመለምላሉ፡፡ ባድዋ ጦርነት ብዙ አዝማሪዎች ማሲንቆ ታጥቀው ዘምተዋል፡፡ አንዳንዶች ለውለታቸው ከድል በኋላ ማእረግና መታሰቢያ ተበርክቶላቸዋል፡፡ማንበብ ይቀጥሉ…

የፍቅረኞች ቀን

የፍቅረኞች ቀንን የማልወደው ፍቅርን ስለማልወድ አይደለም፡፡ ፍቅርን የሚዘክር ቀንን ስለምጠላም አይደለም፡፡ የፍቅረኞች ቀንን የማልወደው ከፍቅረኞች ቀን ይልቅ የጥቅመኞች ቀን እየሆነ ስለመጣ ነው፡፡ ‹‹ከወደድከኝ የፍቅረኞች ቀን እለት ግሎባል ሆቴል ውሰደኝ›› የሚል ማስታወቂያ በየቦታው ተለጥፎ ሳይ፣ ‹‹እኔ ዘንድሮ እንደአምናው በቸኮሌት አልሸወድልህም…ዘንድሮ የምፈልገው የኢቴልኮንማንበብ ይቀጥሉ…

የእቴጌ እና የሂትለር ፎቶ

ባየኋቸው ቁጥር ግርርም ከሚሉኝ ታሪካዊ ፎቶዎች አንዱን ላካፍልዎት፡፡ በ1935 የተነሣው ይህ ፎቶው የተገኘው ባሶሼትድ ፕሬስ መዝገብ ውስጥ ነው፡፡ በፎቶው ላይ ለጊዜው ስሙን ያልደረስኩበት ሠዓሊ የግርማዊት እቴጌ መነን እና የአዶልፍ ሂትለርን ሥዕል ሲሸጥ ይታያል፡፡ በፎቶው ጀርባ ላይ እንደ ተገለጸው ከሆነ፤የጀርመኑ አምባገነንማንበብ ይቀጥሉ…

ባለ መሰንቆውና ባለ ወለሎው

“ሮድ ደሴት” በተባለ አገር ውስጥ እንደ እንደምኖር የነገርኩት ጓደኛየ “እና ባሣ አጥማጅነት ነው የምትተዳደረው?” ብሎኛል፡፡ ሮድ ደሴት አበሻ እጥረት ክፉኛ ከሚያጠቃቸው ክልሎች አንዱ ነው ፡፡ አሁን ምድሩም ሰማዩም ሰውም ነጭ ነው፡፡ ያገር ሰው በጣም ይናፍቀኛል፡፡ የሆነ ያበሻ ዓይነ ውሃ ያለው አልፎማንበብ ይቀጥሉ…

“አልወለድም!” (ክፍል ሁለት)

እየተደናበረች በመሮጥ ላይ ሳለች እንቅፋት መትቷት በሙሉ ሰውነቷ ው-ድ-ቅ ስትል ሁለቱም ተናወጡ፡፡ ዘፈንኑን በድንገት አቆመ፡፡ ‹‹ራበኝ!›› አለች በእንቅፋት የተነደለ አውራጣት ጥፍሯን እያሻሸች፡፡ መድማት ጀምሯል፡፡ ‹‹እኔም ርቦኛል…እማ›› ብሎ መለሰላት፡፡ ዝም ብላ ቁስሏን እና ረሃብዋን ስታስታምም ትንሽ ጊዜ ጠበቀና፤ ‹‹እማ…ደሃ በመሆንሽ ታሳዝኚሻለሽ…ነገር ግን ለኔማንበብ ይቀጥሉ…