ይሄ ቀሳ ግን ስንቱን አሳበደ? ቲክቶክ ምስክሬ ነው፤ የድሮ እብድ ሙዚቃ ቤት በር ላይ ይደንስ ነበር ፤ የዘንድሮ ዲጅታል እብድ ደሞ ሞባይሉ ካሜራ ፊት ይደንሳል ፤ እኔ ራሴን እየታዘብኩት ነው፤ አሁን“ ዘፈን ሃጢአት ነው አይደለም?” በሚል ክርክር ላይ በስካይፒ መሳተፌማንበብ ይቀጥሉ…
አመፅ!!
በለው! በለው! ዛሬ ታሪክ ተሰራ! ከተማውን ባንድ እግሩ አቆምነው!! “ሽጉጥ መትረይሱን አንግቶታል ያ ጥቁር ግስላ ደም ሽቶታል” የሚለውን የአለማየሁ እሼቴን ዘፈን በአለማየሁ ፋንታ ድምፅ እያንጎራጎርሁ ከቤቴ ወጣሁ ፤ ፓርኩ ላይ ስደርስ አንዲት ደርባባ ኤሽያዊት ሰልፈኛ ተዋወቅሁ፤ ከኢትዮጵያ እንደሆንኩ ስነግራት አይኗማንበብ ይቀጥሉ…
ትዝታየ በፎቶ ዙርያ
በልጅነቴ ትዝ ከሚሉኝ መፈክሮች አንዱ “ያልሰራ አይብላ” የሚል ነው። ስራ ብሄራዊ ሀይማኖት ሆኖ ነበር። ይሄ ደግሞ በጊዜው ፎቶ አነሳስ ላይ ሳይቀር ይንፀባረቃል ፤ አንድ ሰው ፎቶ ሲነሳ የሆነ ሰርቶ ማሳያ ነገር ፎቶው ውስጥ ማካተት ነበረበት፤ የቤት እመቤት ከሆነች ጥጥ እየፈተለችማንበብ ይቀጥሉ…
ስለ ፎቶ (ክፍል አንድ)
ልጅ እያለሁ ፎቶ ብርቅ ነበር ፤ ከእናቴ ጋራ የሆነ ግብዣ እሄዳለሁ፤ የቤት እመቤቲቱ ቡናው እስኪፈላ ከግድግዳው ላይ መስኮት የሚያህል ባለፍሬም ፎቶ መስቀያ አውርዳ በዳንቴል ወልወል አድርጋ ትጋብዘናለች። በፎቶው ውስጥ ሚስት ጥበብ ቀሚስ ለብሳ ፤ገብረክርስቶስ ጫማ አድርጋ ቁጢጥ ብላ ትታያለች ፤ማንበብ ይቀጥሉ…
ከባልሽ ሐብታሙን ሽማግሌ ከመረጥሽ በኋላ (ክፍል ሶስት)
አጭር ገመድ ማነኝ ብለሽ ትሄጃለሽ? ስለዚህ የሚስቱን ለቅሶ አትሄጅም ። ቀብሯ ላይ አትገኚም። አቶ ይሄይስ የጠበቀው ቢሆንም ከባድ ሃዘን ላይ ስለሆነ ከሳምንት በላይ አይደውልልሽም። የገባልሽን ቃል ሳያጓድል – ግን ደግሞ ምንም ሳይጨምር መንፈቅ ያልፋል። የመንጃ ፈቃድ አውጥተሸ ኒሳን ጁክ መያዝማንበብ ይቀጥሉ…
ከባልሽ ሐብታሙን ሽማግሌ ከመረጥሽ በኋላ (ክፍል ሁለት)
ያለ ተጨማሪ ጥቅማጥቅም ለተከታታይ ቀናት በግብዣ ያጣድፍሻል። በስጦታ ያንበሸብሽሻል። ምንም ነገር ውድ ነው ከማይል ወንድ ጋር መሆን ምንኛ ያስደስታል? ያየሽውን ሁሉ በሁለትና በሶስት አባዝቶ፣ ያማረሽን ሁሉ በጅምላ ገዝቶ የሚሰጥ ወዳጅ እንዴት ያረካል? ብለሽ ታስቢያለሽ። የቁርስ-ብረንች-ምሳ- እራት ግብዣዎቹ ያልለመድሻቸው አይነት ናቸው።ማንበብ ይቀጥሉ…
ከባልሽ ሐብታሙን ሽማግሌ የመረጥሽ እለት
ከአስራ ሶስት እህት ድርጅቶቹ በአንዱ ውስጥ ጀማሪ የማርኬቲንግ ሰራተኛ ነሽ። ድካሙ ብዙ፣ ደሞዙ ትንሽ ነው። አግብተሻል። የሁለት አመታት ባልሽ ከአመት በፊት ከስራ ከተቀነሰ ወዲህ ስራ ለማግኘት ሳያሳልስ ደጅ ቢጠናም አልሆነለትም። ብዙ ነገር አይሆንለትም። ግንባር ብቻ ሳይሆን ራእይም የለውም። የሚሰራውን ሰርቶ፣ማንበብ ይቀጥሉ…
የታጋቹ ማስታወሻ
ከፀሀይ በታች አሮጌ ነገር የለም ፤ ፀሃይ ራሷ በየሰኮንዱ ትታደሳለች፤ ከእንቅልፌ ተነሳሁ፤ ተንጠራራሁና አይኔን ባይበሉባየ ጠራርጌ ከእምብርቴ በታች ያለውን ቃኘሁት፤ አጅሬ ከኔ በፊት ቀድሞኝ ተነስቱዋል ፤ የዛሬው ደግሞ የተለየ ነው፤ እስክንድር ነጋ ንግግር ባደረገ ቁጥር ባንዲራ ይዞ ከጀርባ እሚቆመውን ሰውየማንበብ ይቀጥሉ…
ዝክረ- ኳራንታይን (ክፍል ሁለት)
ውበት የውበት ሳሎኖች እንደ መድሃኒት መደብሮች፣ የምግብ መሸጫ ሱቆች እና የህክምና ጣቢያዎች ሁሉ ‹‹አንገብጋቢ አገልግሎት አቅራቢ›› ተብለው መመደብ እንደነበረባቸው ያየንበት ጊዜ ነው- ኳራንታይን። የሴቶች ትክክለኛ የጠጉር ቀለም (በአብዛኛው ሽበት) ፣ ትክክለኛው ኪንኪ ጠጉርን (ሂውማንሄር ለረጅም ጊዜ በካውያ ሳይሰራ ሲቀር ተሳስሮማንበብ ይቀጥሉ…
ዝክረ- ኳራንታይን
ከወረርሽኙ መባቻ አንስቶ፤ ‹‹ብትችሉ ከቤት ንቅንቅ አትበሉ›› ከተባለ ጀምሮ፣ መደበኛ የቢሮ ስራቸውን በቢጃማ፣ ቢያሻቸው ሶፋቸው፣ ቢላቸው አልጋቸው፣ ሲያምራቸው መሬት ተቀምጠው በርቀት እንዲሰሩ ከተፈቀደላቸው፣ እድል ከቀናቸው ጥቂት አዲስ አበባዊያን መሃል ነኝ። እግሮቼን ከሰፈር ሳልርቅ ለማፍታታት ወጣ ከማለት፣ ወጥ ወጥ፣ ቤት ቤትማንበብ ይቀጥሉ…