ጎረቤቴ ካለው ቤተክርስትያን የሚመጣው የቅዳሴ ዜማ እና የወፎች ዝማሬ አነቃኝ። እንዴት ውብ አነቃቅ ነው! በሰላም አሳድሮ ይሄንን አዲስ ቀን ስላሳየኝ ምንኛ የታደልኩ ነኝ? ዛሬን ከማያዩት ስላልደባለቀኝ ምንኛ አድለኛ ነኝ? አልጋዬ ውስጥ እንዳለሁ ተንጠራራሁ። ሌላ ጊዜ ቅዳሜ እንደማደርገው አልጋ ውስጥ ስንደባለልማንበብ ይቀጥሉ…
የምንችለውን ወይስ የሚገባንን?
የሚቻለውን መሥራት የዐቅም ጉዳይ ነው። የሚገባውን መሥራት ግን የሕግና የሞራል ጉዳይ ነው። ኃይልን ለመጠቀም የሚያስችል ትምህርት ለሚማሩ ሰዎች በጥብቅ የሚነገራቸው ነገር ቢኖር የተገቢነት ጉዳይ ነው። ካራቴ፣ ጂዶ፣ ቦክስ፣ ውትድርና፣ ፖሊስነት የተማሩ ሰዎች ኃይልን ለመጠቀም ቅርብ ናቸው። በእጃቸው ማጠናፈር፣ በእግራቸው መዘረር፣ማንበብ ይቀጥሉ…
የማርች 8 የስልክ ጥሪዎች…
ማርች 8 መጣሁ መጣሁ ሲል ፤ መቶ እና ከመቶ ሰው በላይ የሚያውቃቸው ሴቶች ስልክ በጥሪ የሚጨናነቅበት ወቅት ነው። እኔም እዚህ ፌስቡክ ላይ መቶ ምናምን ሰው ያውቀኝ የለ? አንድ እሽግ ስሜንም እኔንም የማያውቁ ሰዎች የሚያውቁኝ ሰዎች ፈቃዴን እንኳን ሳይጠይቁ ቁጥሬን ስለሰጡዋቸውማንበብ ይቀጥሉ…
ስለፍቅር በስምአብ ይቅር!!
በዙረት ካገኘሗቸው እውቀቶች አንዱን በማካፈል ወጌን ልጀምር። ያፍሪካ ስደተኞች ያንዱን ያውሮፓ አገር ድንበር አቋርጠው ይገቡና አንድ ከተማ ውስጥ አድፍጠው ይቀመጣሉ። በከተማው ባንድ ስፍራ ላይ መንግስት ገንብቶ ያልጨረሰው ባዶ ህንፃ ይኖራል። ስደተኞች ከለታት አንድ ቀን ተደራጅተው ህንፃውን ወርረው ይይዙታል። የህንፃውን አፓርታማማንበብ ይቀጥሉ…
ሰው በሰውነቱ
የምግብ ቤት ባለቤት የሆነ ሰውየ :በደንበኞቹ መሀል ሲዘዋወር አንድ ዝነኛ ጋዜጠኛ ይመለከታል። ወድያው ባለቤትየው አስተናጋጂቱን ጠርቶ ” እዛ ጥግ ላይ የተቀመጠው ጋዜጠኛ ይታይሻል? ሂጅና የሚፈልገውን እየጠየቅሽ ተንከባከቢው!! ወጥ ካነሰው ጨምሪለት!! እንዲያውም ለኔ ራት ከተሰራው ዶሮ አንድ ቅልጥም ብትሰጪው ደስ ይለኛል።ማንበብ ይቀጥሉ…
ፈገግታ ነው የሚቀድመኝ
የድሜ ነፋስ በገላየ : ተረማምዶ ኮበለለ ልቤን ክንዴን እያዛለ ያቀፍኩትን እየቀማ : የያዝኩትን እያስጣለ። እድል በኔ ጨከነ ስል-በምረት እጅ ደባበሰኝ አንቺ ነጥቆ ከቅፌ ላይ-በትውስታ ደሞ ካሰኝ። አሰታወሰኝ አስታወሰኝ። ወድያው ታይቶ :ጠፊ ኩርፍያሽ ገራም ሳቅሽ : ልዝብ ልፍያሽ ያለም ዘፋኝ የማያውቀውማንበብ ይቀጥሉ…
ጉደኛ ስንኞች
እንዳለመታደል ሁኖ የጎጃሙ ጌታ የራስ አዳል ልጆች አሪፍ ያገር አስተዳዳሪ አልነበሩም። እንደመታደል ሆኖ ደሞ የተዋጣላቸው ባለቅኔዎች ነበሩ። ግጥሞቻቸው ከኑሯችን ጋር በጣም የተቆራኙ ናቸው። ለምሳሌ የግፍ ዘገባ በሰማን ቁጥር የምንቀባበለው። “የለህም እንዳልል ይመሻል ይነጋል አለህም እንዳልል እንዲህ ይደረጋል” የሚለውን ገራሚ ግጥምማንበብ ይቀጥሉ…
ትናንት ዛሬ አደለም
ይገርማል!! ያገራችን ገበሬ የሚያርስበት በሬና ማረሻ ጥንታዊ ሰው ከአራት ሺህ አመት በፊት ይገለገልበት የነበረውን ነው። ይሁን እንጂ ቢቀናው ክላሺንኮቭ ይታጠቃል። ደሞ ገበሬውን ዘመናዊ ጠመንጃ እንጂ ዘመናዊ ማረሻ ለማስታጠቅ የሚያልም አክቲቪስት አይተን አናውቅም። ዘመናይ የብሄር አክትቪስት ጦርነት በናፈቀ ቁጥር ያባቶቹን ጀብድማንበብ ይቀጥሉ…
ተማሪዎችን እንረዳቸው!
የዩንቨርስቴ ተማሪዎች ወገን ለይተው በተደባደቡ ቁጥር ምን አደባደባቸው ብሎ የሚጠይቅ የለም። ከዚያ ይልቅ መስደብ መሸርደድ ማዋረድና ሙድ መያዝ ለምደናል። ባገራችን ከቤተመቅደስ እስከ ስቴድየም ድረስ ጎሰኝነት ያልነካካው ተቁዋም እንደለሌ እናውቃለን። ተማሪዎች ከሌላው የከተማ ነዋሪ የከፋ ጎሰኝነት እንደተሸከሙ የምናረጋግጥበት ሚዛን የለም።ማንበብ ይቀጥሉ…
በኅዳር ውስጥ እኔን
(የነፍሴ ክስ) ተወው! ቆሻሻህን ተወው ከሳቱ ዳር እራቅ ጭለማን ልበሰው ጥቁር ካባ ደርብ ዓይንህ ይጨልመው። … ግዴለህም ተወው እቤትህ ግባና ዓይንህን ጨፍነህ ስላሳመምካቸው ስላቆሰልካቸው ነፍሳት አስብና ራስህን ክሰስ ራስህን ውቀስ ራስህን አጥን ተረማመድበት በንፁሀን ፋና። … የነፍስህን እድፍ የውስጥህን ጉድፍማንበብ ይቀጥሉ…