ትናንት ዛሬ አደለም

ይገርማል!! ያገራችን ገበሬ የሚያርስበት በሬና ማረሻ ጥንታዊ ሰው ከአራት ሺህ አመት በፊት ይገለገልበት የነበረውን ነው። ይሁን እንጂ ቢቀናው ክላሺንኮቭ ይታጠቃል። ደሞ ገበሬውን ዘመናዊ ጠመንጃ እንጂ ዘመናዊ ማረሻ ለማስታጠቅ የሚያልም አክቲቪስት አይተን አናውቅም። ዘመናይ የብሄር አክትቪስት ጦርነት በናፈቀ ቁጥር ያባቶቹን ጀብድማንበብ ይቀጥሉ…

ተማሪዎችን እንረዳቸው!

  የዩንቨርስቴ ተማሪዎች ወገን ለይተው በተደባደቡ ቁጥር ምን አደባደባቸው ብሎ የሚጠይቅ የለም። ከዚያ ይልቅ መስደብ መሸርደድ ማዋረድና ሙድ መያዝ ለምደናል። ባገራችን ከቤተመቅደስ እስከ ስቴድየም ድረስ ጎሰኝነት ያልነካካው ተቁዋም እንደለሌ እናውቃለን። ተማሪዎች ከሌላው የከተማ ነዋሪ የከፋ ጎሰኝነት እንደተሸከሙ የምናረጋግጥበት ሚዛን የለም።ማንበብ ይቀጥሉ…

በኅዳር ውስጥ እኔን

(የነፍሴ ክስ) ተወው! ቆሻሻህን ተወው  ከሳቱ ዳር እራቅ ጭለማን ልበሰው ጥቁር ካባ ደርብ ዓይንህ ይጨልመው። … ግዴለህም ተወው እቤትህ ግባና ዓይንህን ጨፍነህ ስላሳመምካቸው ስላቆሰልካቸው ነፍሳት አስብና ራስህን ክሰስ ራስህን ውቀስ ራስህን አጥን ተረማመድበት በንፁሀን ፋና። … የነፍስህን እድፍ የውስጥህን ጉድፍማንበብ ይቀጥሉ…

ካልፎሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ

ባለፈው ከውጭ ወዳገር ቤት ስመጣ አንዱ ደውሎ:- ” ጀለስካ ወዳገር ቤት ለመግባት ኤርፖርት ታይተሃል የሚባል ነገር ሰማሁ ልበል” ” ልክ ነው!” “በሩ ላይ ጠብቀኝ ታክሲ ይዤ መጣሁ” “እቃ ውሰድልኝ ልትለኝ ባልሆነ?” “ምናለበት ብትቸገርልኝ” ” አዝናለሁ ሻንጣየ ውስጥ ላየር ማስገብያ የሚሆንማንበብ ይቀጥሉ…

እኔ እምፈልገው

እውነት ለመናገር፥እኔ እምፈልገው ካንቺ ጋር መጋባት ይህን ሐምሌ ፊቴን፥ ደጋግሞ ማራባት ከወፎች ጋር መንቃት፥ በጊዜ ቤት መግባት “ምንም ድሀ ቢሆን፥ ባይኖረውም ሀብት ከደጃፍ ሲቀመጥ፥ ደስ ይላል አባት” ለሚል መናኛ ጥቅስ ፥ ኑሮየን ማይመጥን ሲሻኝ በየባንኩ፥ ስፈልግ በሳጥን የተረፈኝ ገንዘብ ደጃፍማንበብ ይቀጥሉ…

ድንኩዋን ሰባሪው

  አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ከድህነት ወለል በታች የሚኖር ነው። የቸሬ ድህነት ግን ወለል እንኩዋ የለውም። ከቸሬ ጋር ስትወዳደር ድህነት ራሷ ሀብታም ናት። እኔ ግን ምናለ መፈላሰፉን ትቼ ወደ ታሪኩ ብገባ ! በቀደምለት ቸሬ ተፈናቃይ ወገኖቻችንን በጉልበትና በፀሎት ለማገዝ ወደ ስፍራውማንበብ ይቀጥሉ…

ወፋ በፌስቡክ

በድሮ ጊዜ በኢትዮጵያ ባንዳንድ ገጠሮች ውስጥ “ወፋ” የሚባል ልማድ ነበር። ያንድ ቀበሌ ባላገሮች ከወንዝ ወዲህ ማዶ እና ወድያ ማዶ ተሰላልፈው በጩቤ በጦር በዱላ ይከሳከሳሉ። አንድ ባላገር ከገበያ ሲመለስ የወፋ ጦርነት ሲካሄድ ከተመለከተ ቆም ብሎ ቅርጫቱን ያስቀምጣል። ከዚያ በቅርብ ከሚያገኘው ጎራማንበብ ይቀጥሉ…

ቅንጥብጣቢ የአስመራ እና የምፅዋ ወግ (ክፍል ሶስት)

አስመራ – ከተወራላት በላይ የምታምረው ከተማ አዲስ አበባ እና አስመራ በብዙ ነገር የተለያዩ ከተሞች ይሁኑ እንጂ በተለይ የድሮዋን አዲስን ለሚያውቅ ሰው የአስመራን መልክ መገመት የሚከብድ አይመስለኝም። እስቲ ድፍን ፒያሳን አስቡ። ብሄራዊ ቲያትር አካባቢን፣ አምባሳደር፣ ኢትዮጵያ ሆቴል አካባቢን ጨምሩ። ሜክሲኮ የድሮውንማንበብ ይቀጥሉ…

ቅንጥብጣቢ የአስመራ እና ምፅዋ ወግ (ክፍል ሁለት)

አስመራ- ከተወራላት በላይ የምታምረው ከተማ ለስድስት ቀን ቆይታዬ በፊልሞን አማካኝነት ወደተያዘልኝ አምባሳደር ሆቴል ገባሁ። የእንግዳ መቀበያውና በኋላ ያየሁት በስተግራ ያለው ሻይ ቤት ነገረ ስራው ሁሉ የፒያሳውን ቶሞካ አስታወሰኝ። ሞቅ ባለ ሁኔታ የተቀበለኝ አስተናባሪ ሻንጣዬን ይዞ ክፍሌን የሚያሳየኝ ጎልማሳ መድቦልኝ አሳንሰሩማንበብ ይቀጥሉ…

ቅንጥብጣቢ የአስመራ እና ምፅዋ ወግ

አስመራ- ከተወራላት በላይ የምታምረው ከተማ ‹‹እናት ብዙ ሻንጣ የለሽም አይደል? እባክሽ ይህቺን ስኳር ያዢልኝ? የእኔ እህት….ኪሎ በዝቶብን ነው…ይህችን ቡና ትይዥልኛለሽ?….እመቤት… ያንቺ አልሞላም አይደል…እባክሽ እነዚህን ጫማዎች ያዢልን…›› እያሉ ብዙ ሰዎች ያዋክቡኛል። ቦሌ አየር ማረፊያ አስመራ የሚወስደኝን አውሮፕላን ለመሳፈር ሻንጣ ማስረከቢያው ጋርማንበብ ይቀጥሉ…