አቶ ሀዲስ አለማየሁ ስለ ኢትዮጵያ ሁኔታ የሰነዘሩዋቸው አስተያየቶች

አቶ ሀዲስ አለማየሁ በልቦለድ ፀሀፊነታቸው የተጋረደ የፖለቲካ ሰብእና ነበራቸው። በተለያየ ጊዜ ስለ ኢትዮጵያ ሁኔታ የሰነዘሩዋቸው አስተያየቶች እንደ ደረቅ ትንቢት የሚቆጠሩ ነበሩ። ለዛሬ: መጋቢት 19: 1985 አመተ ምህረት ባዲሳባ ዩንቨርሲቲ ካቀረቡት ንግግር የሚከተለውን ለመቀንጨብ ወደድሁ። በጥሞና አንብበን በሰከነ መንፈስ እንወያይበት። የንግግሩማንበብ ይቀጥሉ…

የቀበሌ 01 የመጨረሻዋ ድንግል እንደምን አረገዘች!?

(በመጀመሪያ ከላይ የተጠቀሰውን ርእስ ከሁለት ታላላቅ ደራሲዎች የተዋስኩት እንደሆነ ለመግለጽ እፈልጋለሁ።”የቀበሌ 01 የመጨረሻዋ ድንግል” የሚለውን ሀረግ ከአዳም ረታ መጽሃፍ የተዋስኩት ሲሆን “እንደምን” የሚለውን ቃል ደግሞ “ጃፓን እንደምን ሰለጠነች?” ከሚለው የከበደ ሚካኤል መጽሃፍ የወሰድኩት ነው።”አረገዘች” የሚለው ቃል እና የጥያቄ ምልክቱ(?) ግንማንበብ ይቀጥሉ…

ድልድዮቹን ተውልን

እመሃል ላይ ተገምሰው ማዶ ለማዶ የሚያተያዩን ሰባራ ድልድዮች እየበዙ ነው… አንዳንዶቹን ሆን ብለን ሰብረናቸዋል… አንዳንዶቹ በሌሎች ሰንኮፎቻችን ዳፋ ተሰብረዋል… ሌሎቹን ግን መሰበራቸውን እንኳ አልተረዳንም… ~ አንዳንዶች የሚሰብሩትን ድልድይ ፋይዳ በወቅት ስሜታቸው ትኩሳት ውስጥ ብቻ ስለሚመዝኑ የሰባሪነት ወኔ እንጂ የአስተዋይነት ስክነትማንበብ ይቀጥሉ…

ራሴው ማበዴ ነው (ክፍል አምስት)

“ራሔል ከዚህ በላይ እናትሽን እቤት ልታቆያቸው የምትችዪ አይመስለኝም። አደገኛ ነው የሚሆነው።” “ዶክተር በፍፁም ሆስፒታል እንደማልተዋት ቃል ገብቼላታለሁ። አይሆንም!! ታውቅ የለ ምን ያህል እንደምትጠላ?” “ራሔል እስቲ ተቀመጪ።” አለኝ ወንበሩን እያሳየኝ። በእማዬ ምክንያት ከማውቀው ልምድ በዶክተሮች አባባል ‘እስኪ አረፍ በይ፣ እስኪ ተቀመጪ፣ማንበብ ይቀጥሉ…

ልጅነቴን አፋልጉኝ

ማደግ በመሰለኝ ረግረግ ውስጥ የጠፋች ልጅነቴን አፋልጉኝ – ማወቅ በመሰለኝ ጥልቅ ውስጥ የተደበቀች ልጅነቴን አፋልጉኝ – ከድቅድቅ ጽልመት ውስጥ የዘነጋሁዋትን እውነት አፋልጉኝ… ~ ዕድሜ የሥጋ ኑረት መስፈሪያ እንጂ የውዷ ሕይወት መግለጫ አይደለም… ሕይወቴ ልጅነቴ ነው… ዕድሜ ደግሞ የልጅነቴን ንጽሕና የነጠቀኝማንበብ ይቀጥሉ…

ጠፍታ አገኘችኝ

የደመናው ጽልማሞት በዝናብ ፍርሃትና በቀጠሮ አለማክበር ስጋት መሃል አዕምሮዬን እያላጋብኝ ወደ ታክሲ መያዣው የማደርገውን ግስጋሴ ትቼ ቅርቤ ወዳለ ካፌ ዘለቅሁ… ፒያሳ ነኝ… ከመቀመጤ ሸገር እሪ ብላ አነባች… በጣም ከባድ ዝናብ መውረድ ጀመረ… “ሸበሌ እንገናኝ” ነበር ያለችኝ… ፍቅረኛዬ ናት… ‘ጥብቅ ጉዳይ’ማንበብ ይቀጥሉ…

ብርሃን ፍለጋ

ወይንሸት የመጀመርያ ልጅ ነች። ዕድሜዋ አስር ሆኗል። እኩዮቿ ከክፍል ወደ ክፍል በተዘዋወሩ ቁጥር እሷ ግን ታናናሾቿን በመሸከም ነው ከዓመት ወደ ዓመት የምትሸጋገረው! ወላጆቿ ሞግዚት የመቅጠር አቅም የላቸውም፤ ለዚህም ነው ወይንሸትን ወደ ፊደል ገበታ ያልሰደዷት። አባቷ ‘ሰርቶ በይ!’ የሚል ድምፅ ወደሰማበትማንበብ ይቀጥሉ…

እድሜዬ እና የኢትዮጲያ እርምጃ!

ሰላም ነው ጋይስ! እንግዲህ ቅዳሜ እለት በከፍተኛ ድምቀት ተከብሮ ያለፈውን የ 35ኛ አመት የልደት በአሌን በማስመልከት ብዙዎች ” እድሜህ ስንት ነው?” በማለት በጠየቃችሁት መሰረት ስለ እድሜዬ የሚከተለውን መግለጫ ለመስጠት ተገድጃለሁ። ግና ለአንባቢ የተወለድኩበትን ዓመተ ምህረት በቀጥታ ከመናገር ይልቅ እስከዛሬዋ እለትማንበብ ይቀጥሉ…

ራሴው ማበዴ ነው (ክፍል አራት)

“ልትነግሪኝ የምትፈልጊው ነገር አለሽ?” “ማለት? ስለምን?” “እኔ እንጃ ቦስ አባትሽ እዚህ ቢሮ እግራቸው ከረገጠ ቀን ጀምሮ ላለፉት ሁለት ሳምንታት ፍፁም ልክ አይደለሽም። ያዘንሽ ያዘንሽ ፣ የተከፋሽ ፣ የሆነ ነገር ያደከመሽ አይነት ነው የምትመስዪው።” ሲለኝ ለቅፅበት ያደከመኝን ሁሉ ልነግረው ዳድቶኝ ነበር።ማንበብ ይቀጥሉ…

“ስለ ቅዳሜ ሲባል ስለ ‘ሁድ ካወራን ተሳስተናል!”

እኔን መምከርና መርገም አሪፍ የስተርጅና ጊዜ መደበርያ ከሆነለት ከፋዘር ጋር እንደተለመደው ሶስት ከባድ የምክር እና የተግሳፅ ሰኣታትን አሳለፍኩ።እንዳረዛዘሙ አመታትን ብል ይቀለኛል ለነገሩ።የማዘርን ጉሽ ጠላ በላይ በላይ እየነፋ፣የአተላውን ግርድፍ በላዬ ላይ እየተፋ መጠጥ እርም እንድል ካልተሳሳትኩ ለመቶ አስራ ሰባተኛ ጊዜ ዛሬምማንበብ ይቀጥሉ…