“ራሔል ከዚህ በላይ እናትሽን እቤት ልታቆያቸው የምትችዪ አይመስለኝም። አደገኛ ነው የሚሆነው።” “ዶክተር በፍፁም ሆስፒታል እንደማልተዋት ቃል ገብቼላታለሁ። አይሆንም!! ታውቅ የለ ምን ያህል እንደምትጠላ?” “ራሔል እስቲ ተቀመጪ።” አለኝ ወንበሩን እያሳየኝ። በእማዬ ምክንያት ከማውቀው ልምድ በዶክተሮች አባባል ‘እስኪ አረፍ በይ፣ እስኪ ተቀመጪ፣ማንበብ ይቀጥሉ…
ልጅነቴን አፋልጉኝ
ማደግ በመሰለኝ ረግረግ ውስጥ የጠፋች ልጅነቴን አፋልጉኝ – ማወቅ በመሰለኝ ጥልቅ ውስጥ የተደበቀች ልጅነቴን አፋልጉኝ – ከድቅድቅ ጽልመት ውስጥ የዘነጋሁዋትን እውነት አፋልጉኝ… ~ ዕድሜ የሥጋ ኑረት መስፈሪያ እንጂ የውዷ ሕይወት መግለጫ አይደለም… ሕይወቴ ልጅነቴ ነው… ዕድሜ ደግሞ የልጅነቴን ንጽሕና የነጠቀኝማንበብ ይቀጥሉ…
ጠፍታ አገኘችኝ
የደመናው ጽልማሞት በዝናብ ፍርሃትና በቀጠሮ አለማክበር ስጋት መሃል አዕምሮዬን እያላጋብኝ ወደ ታክሲ መያዣው የማደርገውን ግስጋሴ ትቼ ቅርቤ ወዳለ ካፌ ዘለቅሁ… ፒያሳ ነኝ… ከመቀመጤ ሸገር እሪ ብላ አነባች… በጣም ከባድ ዝናብ መውረድ ጀመረ… “ሸበሌ እንገናኝ” ነበር ያለችኝ… ፍቅረኛዬ ናት… ‘ጥብቅ ጉዳይ’ማንበብ ይቀጥሉ…
ብርሃን ፍለጋ
ወይንሸት የመጀመርያ ልጅ ነች። ዕድሜዋ አስር ሆኗል። እኩዮቿ ከክፍል ወደ ክፍል በተዘዋወሩ ቁጥር እሷ ግን ታናናሾቿን በመሸከም ነው ከዓመት ወደ ዓመት የምትሸጋገረው! ወላጆቿ ሞግዚት የመቅጠር አቅም የላቸውም፤ ለዚህም ነው ወይንሸትን ወደ ፊደል ገበታ ያልሰደዷት። አባቷ ‘ሰርቶ በይ!’ የሚል ድምፅ ወደሰማበትማንበብ ይቀጥሉ…
እድሜዬ እና የኢትዮጲያ እርምጃ!
ሰላም ነው ጋይስ! እንግዲህ ቅዳሜ እለት በከፍተኛ ድምቀት ተከብሮ ያለፈውን የ 35ኛ አመት የልደት በአሌን በማስመልከት ብዙዎች ” እድሜህ ስንት ነው?” በማለት በጠየቃችሁት መሰረት ስለ እድሜዬ የሚከተለውን መግለጫ ለመስጠት ተገድጃለሁ። ግና ለአንባቢ የተወለድኩበትን ዓመተ ምህረት በቀጥታ ከመናገር ይልቅ እስከዛሬዋ እለትማንበብ ይቀጥሉ…
ራሴው ማበዴ ነው (ክፍል አራት)
“ልትነግሪኝ የምትፈልጊው ነገር አለሽ?” “ማለት? ስለምን?” “እኔ እንጃ ቦስ አባትሽ እዚህ ቢሮ እግራቸው ከረገጠ ቀን ጀምሮ ላለፉት ሁለት ሳምንታት ፍፁም ልክ አይደለሽም። ያዘንሽ ያዘንሽ ፣ የተከፋሽ ፣ የሆነ ነገር ያደከመሽ አይነት ነው የምትመስዪው።” ሲለኝ ለቅፅበት ያደከመኝን ሁሉ ልነግረው ዳድቶኝ ነበር።ማንበብ ይቀጥሉ…
“ስለ ቅዳሜ ሲባል ስለ ‘ሁድ ካወራን ተሳስተናል!”
እኔን መምከርና መርገም አሪፍ የስተርጅና ጊዜ መደበርያ ከሆነለት ከፋዘር ጋር እንደተለመደው ሶስት ከባድ የምክር እና የተግሳፅ ሰኣታትን አሳለፍኩ።እንዳረዛዘሙ አመታትን ብል ይቀለኛል ለነገሩ።የማዘርን ጉሽ ጠላ በላይ በላይ እየነፋ፣የአተላውን ግርድፍ በላዬ ላይ እየተፋ መጠጥ እርም እንድል ካልተሳሳትኩ ለመቶ አስራ ሰባተኛ ጊዜ ዛሬምማንበብ ይቀጥሉ…
ራሴው ማበዴ ነው (ክፍል ሁለት)
“አቤት?” አልኩት ለሰላምታ የዘረጋውን እጁን ችላ ብዬ ወንበሬ ላይ እየተቀመጥኩ። ፀጉሩ አልፎ አልፎ ከመሸበቱ ውጪ ብዙም አልተለወጠም። “ደህና ነሽ ሚሚሾ?” “ምን ፈልገህ ነው የመጣኸው? ደህና መሆኔ አሳስቦህ አይሆንም መቼም!! የልጅህ ሰርግ ጥሪ ወረቀት እንደደረሰኝ ለማረጋገጥ ከሆነ ደርሶኛል። እማም ደርሷታል። ጨርቄንማንበብ ይቀጥሉ…
ራሴው ማበዴ ነው
“ተሳፋሪዎቻችን ይህ የበረራ ቁጥር 206 ነው… … ” ጭንቅላቷ እየሸወዳት እንደሆነ የማውቀው እንዲህ ማለት ስትጀምር ነው። በግልቡ እብደቷ እየጀመራት ነው ማለት ነው። እናቴ ናት!! ይሄን ሀረግ ማለት ከጀመረች ትርጉሙ የዛሬ 20 ዓመት ወደ ኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሆስተስ የነበረችበት ዘመንማንበብ ይቀጥሉ…
በውበት ሳሎኑ ውስጥ – 3
ውድ አንባብያን! <ያልተቀበልናቸው>የተሰኘው አዲሱ መጽሐፌን በየመጻሕፍት መደብሩና በየአዙዋሪዎቹ እጅ ታገኙታላችሁ።መጽሐፉ በእጃችሁ እስኪገባ፣አሁንም አንድ ቁንጽል ጻሪክ ከመሐፉ ልጋብዛችሁ። በውበት ሳሎኑ ውስጥ – 3 ——- የተቀመጥኩት መግቢያው በር አጠገብ ነበር። የሆነ ሰው፣ እጀርባዬ እንደቆመ ትከሻዬ ነግሮኝ ቀና አልኩ። ቀና ስል፣ ከዚህ ቀደምማንበብ ይቀጥሉ…