ፓለቲካ አልወድም። የማልወደው፣ ሰዎች የሚያንቀሳቅሱት ሳይሆን ሰዎችን የሚያንቅሳቅሳቸው ስለሆነ ነው። ፓሊዮ እና ዚካ ተቀላቅለው የፈጠረቱ ይመስለኛል። የጠላሁት ቤቴ ገባ። አትግባ እንዳልለው፣ ይዛው የገባችው ባለቤቴ ናት። መች እንደጀመራት ሳላውቅ ፓለቲካ አተኮሳት። ቀጥሎ አነደዳት። ተቃጠለች። እሳቷ እሳቴ ሆነ። ፍቅር ከሰራን በኋላ ሁሉ፣የአደረግነውንማንበብ ይቀጥሉ…
ሌላ ፓለቲከኛ ሚስት አገባሁ
ይቅርታ! ፓለቲከኛ ያልኩት ተሳስቼ ነው። የአሁኗ ሚስቴ ሃይማኖተኛ ናት።ፓለቲካኛ ያልኩት በቀደመው ትዳሬ ተፅዕኖ ነውና ይቅር በሉኝ። የአሁኗ ሚስቴ ጴንጤ ናት። አንድ ሰው ታሞ እያጣጠረ ብታገኝ፣ ራበኝ እያለ አጠገቧ ቢያጣጥር አንድ ጉርሻ በመስጠት ፈንታ«ቆይ አንዴ ልፀልይለት ብላ እጇን በላዩ ላይ» የምትጭንማንበብ ይቀጥሉ…
ለቅምሻ የተቀነጨበ
…..ብዙው ኢትዮጲያዊ የራሱን ነፍስ ኑሯት አያውቅም … ከልጅነት እስከእውቀት ለሌሎች ይኖራል ! ወዶ ሳይሆን ተገዶ !! ሙሉ ደሞዙን ደስ ብሎት ተጠቅሞበት የሚያውቅ ማነው ? …. ለዛ ነው ኢትዮጲያ ውስጥ ኑሮ ‹‹መቀማት ›› የሆነው ……የምትረዳውን ሰው ወደድከውም አልወደድከውም መርዳት ግዴታህም ይሁንማንበብ ይቀጥሉ…
የነፍጠኞች ፖሊቲካ
ነፍጠኛነት ባህላችን ነው፤ ፖሊቲከኛነት አዲስና ባዕድ የትግል ዘዴ ነው፤ ፖሊቲከኛነትና ነፍጠኛነት ተቃራኒ ተግባሮችን ያመለክታሉ፤ ተቃራኒ ተግባሮች አብዛኛውን ጊዜ ተቃራኒ ዘዴዎች ያስፈልጋቸዋል፤ ለምሳሌ መፍጨትና መቡካት ተቃራኒ ተግባሮች ናቸው፤ መፍጨት ሲበታትን፣ ማቡካት ሰብስቦ ያያይዛል፤ የሚፈጭ ሰው ማቡካት ይችላል፤ እንዲሁም ማቡካት የሚችል ሰውማንበብ ይቀጥሉ…
ማዘሎ !!
በእድሜ የገፉ ሰዎችን ማክበር ጥሩ ነው ! ከሞራልም ከሃይማኖትም አንፃር ማለቴ ነው …. ግን እውነታውን እናውራ ከተባለ ስንት የሚያበሳጭ ‹‹ትልቅ ሰው›› አለ መሰላችሁ ምንም የሽምግልና ለዛ የሌለው …ከምር ! አንዳንዴ ወጣት ሁኖ ባጠናፈርኩት ኖሮ የምትሉት እድሜው የትየለሌ የሆነ ሰው አለማንበብ ይቀጥሉ…
ትውስታ… ጋሽ አዳሙ ዘብሔረ አዲስ አበባ!
ይሄ ሁሉ ለሶስት ጥይት ነው ?? የዛን ሰሞን አሜሪካ በሚገኘው የኢትዮጲያ ኤምባሲ በተነሳ ተቃውሞ የኤምባሲው ጠባቂ ሽጉጥ ወደሰማይ ተኩሶ በ48 ሰዓት ከአሜሪካ እንዲባረር በተወሰነበት ሰሞን ጋሽ አዳሙ የሰፈራችን ታዋቂ ሰካራም ….ማታ አራት ሰዓት ላይ እየዘፈነ ብቻውን እያወራ እየተሳደበና እያመሰገነ ሲመጣማንበብ ይቀጥሉ…
ሸውራራ ፌሚኒዝም
ወደ ኋላ ስናይ! አባት እናቶቻችን ባለ ብዙ ስህተት ነበሩ።እንደ አብዛኛው ህዝብ።በብዙ ጉዳዮች ላይ የነፃነት አስተሳሰብን አልተከሉልንም።ትልቁ የጥሩነት መለኪያቸው፣ ለታላላቆች ቃል መገዛት፣ባህል እና ልማድን መጠበቅ ወዘተ እንጂ የልጆቻቸውን intellect በመገንባት ላይ ደካማ ነበሩ። የሚያከራክረን አይመስለኝም። ወደ ኋላ ስናይ፣ ከአሉታዊ ማህበረሰባዊ ጠባያችንማንበብ ይቀጥሉ…
ሞደ ጠባብነት፣ ከጎሳ እስከ ሀገር
«ሞደ ጠባብነት፣ ከጎሳ እስከ ሀገር… ሀንገር በጠለፋት መንደር » 😉 ፌቡም የጎጠኞች መዲና ሆናለች። ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አንፃር ሲነፃፀር የትየለሌ ጨምሯል። ብዙ የቡድናቸው አሳቢዎች አልፎ አልፎ በመግባባት፣ ብዙ ጊዜ በመፈነካከት በዚህች መዲና ይኖራሉ። ጎሳህ ማንነት ነው የሚሉ ድምፆች ይጮሃሉ። ሎልማንበብ ይቀጥሉ…
አይኔን በሌላ ሰው አይን ሳየው
ፍቅረኛየ በየቀኑ እንዲህ ትለኛለች “ አብርሽ ‹የ› ” በቃ ‹ የ› ከጨመረች ጥያቄዋ ምን እንደሆነ አውቀዋለሁ …ቢሆንም እንደአዲስ ነገር ለመስማት “ወይየ” እላለሁ “በናትህ ልጅ እንውለድ ” የሄው አላልኳችሁም ..አቤት ልጅ ስትወድ ! “የኔ ማር ልጅ ምን ይሰራልሻል ?” “ልጅ እኮማንበብ ይቀጥሉ…
አይዳ ለምን ከግቢ እንዳትወጣ ተከለከለች ?
አባ በድሉ ‹‹ድግምተኛ ናቸው ››!! ይቅርታ ‹‹ድግምተኛ ናቸው እየተባለ ይወራል !! እኛ ሰፈር ስትመጡ በጎሚስታው ጋ ወደቀኝ ታጥፋችሁ ፒስታ መንገዷን (አሁን ኮብል ስቶን ተነጥፎበታል) እሷን ይዛችሁ ወደላይ ትንሽ እንደሄዳችሁ …. ዙሪያውን በግንብ የታጠረ የግንብ አጥሩ ደግሞ ሙሉውን ነጭ ቀለም የተቀባማንበብ ይቀጥሉ…