ዶሮዎች ለእኛ ምን አደረጉ ብላችሁ ከመጠየቃችሁ በፊት

ዶሮዎች ለእኛ ምን አደረጉ ብላችሁ ከመጠየቃችሁ በፊት፥ እኛ ለዶሮዎች ምን አደረግንላችው ብላችሁ ጠይቁ፤ በቀደም አንዱ ጉዋደኛችን ሊያገባ እጮኛው ቤት ሽምግልና ተላክን ገና ገብተን ወንበራችን ላይ ሳንደላደል “ ልጁ ምን አለው?” አሉ አባትየው ፤ ከጉዋደኞቻችን አንዱ ኮራ ጀነን ብሎ መለሰ፤ “ልጁማንበብ ይቀጥሉ…

ስለትግራይ ሲነሳ ብዙ ይነሳል

እኔ ጭሮ አዳሪ ስለሆንኩ መጀመርያ የማስታውሰው የፅሁፍ ሰዎችን ነው፤ አለቃ ተወልደ መድህን ፤ ደብተራ ፍስሀ ወልደጊዮርጊስ ፥ ገብረህይወት ባይከዳኝ ፤ ስብሀትለአብ ገብረእግዚአብሄር ፥ ከትግራይ ምድር የተሰጡኝ የኢትዮጵያ ገፀበረከቶች ናቸው። ከ ሶስት መቶ አመት በፊት የተፃፈ የታሪክ ድርሳን አግኝተህ ብታነብ ትግራይማንበብ ይቀጥሉ…

ምርመራ

በቀደምት ቴክሳስ ከተማ የበረዶ ውሽንፍር ጥሎ የከተማው መብራት ተቁዋረጠ፤ በማግስቱ የከተማው አስተዳዳሪ ደውሎልኝ ለከተማው ህዝብ ልምድ እንዳካፍል ጋበዘኝ። “ያለመብራት የመኖር ጥበብ“ እሚል ጥናታዊ ፅሁፍ አዘጋጀሁና ናሙናውን ላክሁለት፤ በጣም ተደስቶ መጠኑን እዚህ ገፅ ላይ የማልገልፀውን ቀብድ ላከልኝ ፤ በህይወቴ ለመጀመርያ ጊዜማንበብ ይቀጥሉ…

‘The past is a foreign country’ (ያለፈው ዘመን ባዕድ አገር ነው)

ይሄን የእንግሊዝኛ ተረት በዚህ ዓመት ውስጥ ሺህ ጊዜ ሳልሰማው አልቀርም። ግን መደጋገሙ ሲበዛብኝ፤ አባባሉ እንዲወደድ ስልት ያለው የማለማመጃ ዘመቻ ወጣቱ ላይ እየተሰራ መሰለኝ። ዘይቤውን የሚናገሩት ብዙ የጥቁር ሀበሻ (ሀበ) ፈረንጃዊያን ብቅ ብለዋል። እነሱም ʻየአገራችንን መልካም ታሪክ እንጥቀስʼ ስንል ዐይኖቻቸው ቀልተውማንበብ ይቀጥሉ…

በርበሬ

“አንድ ወዳጄ . . . በርበሬ ኢትዮጵያዊ ቅመም እንዳልሆነና ሲጀመር በአስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን በግራኝ ወረራ ጊዜ ፖርቹጋሎች ወደዚህ ሀገር እንዳመጡት ተናገረ . . . ነገሩ እየከበደ ውይይቱ አስደሳች ገፅ አበጀ። ጓደኛዬን ‘በርበሬ ከፖርቹጋል እንደመጣ፤ ምን ማስረጃ አለህ?’ አልኩት። እሱምማንበብ ይቀጥሉ…

ጎበዝ ! እየቀላቀልን እንጂ!

የሆነ ጊዜ ላይ አንዲት ቆንጅየ ልጅ ፍሬንድ ሪኩየስት ላከችልኝ! በእህትነት ተቀበልኳት ! ትንሽ ቆይቼ እህትነቱን ባንድ እርምጃ ላሳድገው ብየ በማሰብ በኢንቦክስ “ ሰፈርሽ የት ነው? አላማስ አለሽ? ” ምናምን ማለት ጀመርሁ ፤ ጥቂት እንዳወጋሁት ግን በሴት ፎቶ የተጠለለ ወንድ መሆኑንማንበብ ይቀጥሉ…

ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ (ክፍል ሰባት)

“አልቻልኩም። …. አልቻልኩም!” ሁለት እጆችዋን ጨብጣ ደረቴን እየደበደበች ታለቅሳለች። ጉንጮቿ እና ከንፈርዋ ይንቀጠቀጣሉ። አንጀት የራቀው ሆድዋ ይርበተበታል። እየደጋገምኩ “እሺ” ከማለት ውጪ የምለው አጣሁ። ድብደባዋን ስታበቃ ንፁህ ያልሆነው መሬት ላይ በነጭ ሱሪዋ ተቀመጠች። “ላናግርህ እፈልጋለሁ” ብላ ሱቋ ጠርታኝ ነው ሱቁን ዘግታማንበብ ይቀጥሉ…

ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ… (ክፍል ስድስት)

“እስክትወስን እጠብቃታለሁ።” ይለኛል። ሁሌም የምንገናኝበት ቦታችን ‘የምናውራው አለ’ ብሎኝ ተገናኝተኝ የጀበና ቡናችንን እየጠጣን። “እኔስ? በፍቅርህ የነሆለለ ጅል ልቤስ? ምን ላድርገው? እስከመቼ ጠብቅ ልበለው? ከሚስቱ እስኪታረቅ ልበለው እስኪለያይ? ንገረኝ የቱን ነው የምጠብቀው?” እንባዬ የአይኔን ድንበር አልፎ ተንዠቀዠቀ። ይሄን ያልኩት ብዙ ስለሷማንበብ ይቀጥሉ…

ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ… (ክፍል አምስት)

“እናውራ? ማውራት አለብን!” አለኝ አምስት ለሊቶች ሳይነካካኝ አቅፎኝ ካደረ በኋላ። አምስት ጠዋቶች ከንፈሬን ሳይስመኝ ደህና ዋዪ ካለኝ በኋላ። አምስት አመሻሾች ደረቱ ላይ አቅፎ ግንባሬን ሳይስመኝ እንዴት ዋልሽ ካለኝ በኋላ…. “Finally” አልኩኝ ይህን እንዲለኝ ስጠብቅ እንደነበር በደንብ እያሳበቅኩ “እንዴ? እንድናወራ እየጠበቅሽማንበብ ይቀጥሉ…

ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ… (ክፍል አራት)

ባሌን እንዲህ እፍፍፍ ያስደረገችውን ሴት ለማየት “የተለመደ” ቦታቸው ባሌን ተከተልኩት። ከስራ እኔን እቤት ካደረሰ በኋላ ነው የወጣው። የጀበኛ ቡና የሚሸጥበት ቤት? ይሄ ነው የተለመደ ቦታቸው? መኪናውን አቁሞ ወረደ። ታክሲውን አስቁሜ በዓይኔ ተከተልኩት። ከተቃራኒ አቅጣጫ እየመጣች ከነበረች ሴት ጋር በፈገግታ ተጠባበቁ።ማንበብ ይቀጥሉ…