የዘውግ ፖለቲካ እንደ ሀገር?

ወደ 25 ሀገሮች ፌደራሊዝምን ይከተላሉ ይላል አሰፋ ፍስሃ ስለ ፌደራሊዝም በፃፈው መፅሐፍ። ያዋጣቸውን አዋጥቷቸው ይሆናል። የኛ ግን የቆመበት መሰረት በራሱ «ፀብ ለሚሹ የሜዳ ጠረጋ» ስለሆነ አልተሳካም ብንል አያኳርፍም። የዘውግ ፖለቲካ አያዋጣም ሲባል እንዲሁ ሳስበው ደስ አይለኝም ከሚል የሚሻገር ሰበብ አለው።ማንበብ ይቀጥሉ…

የኩባያ ወተት ወይስ የኩባያ ውሃ?

ስመጥሩ የእስልምና ታሪክ ተመራማሪና ፀሃፊ አህመዲን ጀበል ለ‹‹ከመጋቢት እስከ መጋቢት›› በተቀረፁት አጭር ቪዲዮ ላይ የተጠቀሟት ታሪክ ደስ አለችኝና አመጣሁላችሁ። ታሪኳ እንዲህ ትላለች። አንድ መሪ ህዝቡ ምን ያህል እንደሚወደው ለማውቅ ፈለገና አደባባይ ላይ ትልቅ በርሜል አስቀምጦ ህዝቡን እንዲህ ብሎ አዘዘ። ‹‹የሚወደኝማንበብ ይቀጥሉ…

የገደለ አባትሽ የሞተው ባልሽ (ክፍል ሶስት)

አማላይ ከሬሳ ሳጥኑ አጠገብ አልነሳም ብላ ለያዥ ለገናዥ አስቸገረች… ጋሼ የልጄ ገዳይ እሷ ናት ካልገደልኳት ብሎ ሁከት አስነሳ። እማዬም ለዓይኔ አልያት አለች። እኔስ? … እኔ ዞረብኝ። «አስወጡልኝ ይህቺን ልጅ… ለልጄ በቅጡ ላልቅስለት አስወጡልኝ! » እማዬ እሪሪሪ አለች። «ይግደሉኝ!… ይግደሉኝ እንጂማንበብ ይቀጥሉ…

‹አንበሳው› ማን ነው፤ ‹አህያውስ› የምን ምሳሌ?

አንበሳን የማምለክ አባዜ በየጉዳዮቻችን ውስጥ ገንኖ ይታያል፤ የምንወዳቸውና የምንፈራቸው ነገሮች በ‹አንበሳ› ስም እንዲጠሩ እንፈልጋለን፤ የሚያገሱ በሚመስሉ የአንበሳ ሀውልቶች ታጥረን መኖር እንፈልጋለን! በተቃራኒው ደግሞ፤ አህያን እዩት፤ የውርደት ምልክት ነው፤ አንድም ቦታ ጠላቶቹን ድል ስለማድረጉ የሚተርክ ተረት አጋጥሞኝ አላነበብኩም ፤ በተረቱ ውስጥማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹አብሮ አይሄድም››

  ለስብሰባ ከመጣች ኖርዌያዊት የስራ ባልደረባዬ ጋር የባጥ የቆጡን እየቀባጠርን ነበር። ኢትዮጵያንም አፍሪካንም ስታይ የመጀመሪያዋ ነው። ምሳ ደረሰና ቡፌው ጋር ስንሄድ፣ ገበታው የጸም እና የፍስክ በሚል መከፈሉን ስታይ ተከታታይ ጥያቄዎች አዘነበችብኝ። ‹‹ብዙ ሰው ይጾማል?›› ‹‹ምን ያህሉ ሰው ኦርቶዶክስ ነው?›› ‹‹ምንማንበብ ይቀጥሉ…

የገደለ አባትሽ… የሞተው ባልሽ (ክፍል፦ ሁለት)

አሚዬ ከእህቴም በላይ ናት።…… አባቷ ወንድሜን ከገደለው እለት ጀምሮ እሷ የኛ ቤተሰብ አካል ሆናለች… የወንድሜ ምትክ.…… የሚያውቀን ሁላ ለዓመታት ከእንጀራው ጋር አብሮ ስማችንን አላመጠው፣ ጎረቤት ከተጣጡት ቡናቸው ጋር ስማችንን አብረው አድቅቀው… አፍልተው ጠጡት… እንዴት ከገዳያቸው ጋር ይወዳጃሉ? ሰው ጠላቱን እንዴትማንበብ ይቀጥሉ…

የገደለ አባትሽ የሞተው ባልሽ

«ወንድ ልጅ አይደለህ እንዴ? እንዴት ፖለቲካ አትወድም?» ብላኝ አረፈችው። እሰይ! «እዚህ ሀገር ከፖለቲካ ጋር ያልተነካካ ብቸኛ ገለልተኛ አካል የኔ አክሱም ነው። ተያ!…… የፓርላማ ጭብጨባ ካልሰማሁ አልቆምም ብሎ አያውቅም። አያደርገውም! እዝህች ሀገር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ በረደ ብሎ ለግሞብኝም አያውቅም። ሽለላ ቀረርቶማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹የድሬ ሰው ነፍሴ››

  የሚያንገረግበውን የድሬ ሙቀት መብረድ ጠብቄ አመሻሹን ሻይ ልጠጣና በእግሬ ወዲህ ወዲያ ልል ከሆቴሌ ወጣሁ።  ለብ ባለው ንፋስ እየተደሰትኩ፣ ቱር ቱር በሚሉት ባጃጆች ካለጊዘዬ ላለመቀጨት እየተጠነቀቅኩ ከተዘዋወርኩ በኋላ ለሻይ አንዲት ትንሽ ቤት ቁጭ አልኩና ምን ይምጣልሽ ስባል ‹‹ቀጭን ሻይ›› ብዬማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹እታባዬ…እታባዬ!›› 

ባለፈው ሰሞን አንድ ቀብር ሄጄ ነው። ሟች፣ እታባ ጠና ያሉ ሴት ነበሩ። የእኛ ሰው ቀጠሮ የሚያከብረው ቀብር ሲሆን ብቻ አይደል? ምን ማክበር ብቻ? ቀድሞ ይጀምራል እንጂ! ያጣድፈዋል..ያዋክበዋል እንጂ! ስለዚህ ለስድስት ሰአት ቀብር መንገድ ተዘጋግቶብኝ እንዳላረፍድ ሰግቼ ከአምስት ሰአት በፊት ከቢሮማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹በሃገር ነው››

ጎረቤቴ ካለው ቤተክርስትያን የሚመጣው የቅዳሴ ዜማ እና የወፎች ዝማሬ አነቃኝ። እንዴት ውብ አነቃቅ ነው! በሰላም አሳድሮ ይሄንን አዲስ ቀን ስላሳየኝ ምንኛ የታደልኩ ነኝ? ዛሬን ከማያዩት ስላልደባለቀኝ ምንኛ አድለኛ ነኝ? አልጋዬ ውስጥ እንዳለሁ ተንጠራራሁ። ሌላ ጊዜ ቅዳሜ እንደማደርገው አልጋ ውስጥ ስንደባለልማንበብ ይቀጥሉ…