ወዲህ በዳዊት ወዲህ በጋሻ!!!

ትላንትና ከባልንጀራየ ምኡዝ ጋር ተገናኝተን ቢራ ወይንና የመሳሰሉትን አልኮሎች ስንጠጣ:-አገርን በፍቅር ስለማስተዳደር አሰፈላጊነት ” በሰፊው ሰበክሁለት። እሱ እያዛጋና እየተቅበጠበጠ ሲሰማኝ ቆይቶ ሳያስጨርሰኝ የሚከተለውን ቀደዳ ቀደደ። “ማኪያቬሊ ስለተባለ ዝነኛ ደራሲ ሰምተህ ይሆን? ስለስልጣን ባህርይ እንደ ሌሎች ሳያለባብስ እቅጯን ፅፏል!! ይህ ሀቀኛማንበብ ይቀጥሉ…

ፈገግታ ነው የሚቀድመኝ 

የድሜ ነፋስ በገላየ : ተረማምዶ ኮበለለ ልቤን ክንዴን እያዛለ ያቀፍኩትን እየቀማ : የያዝኩትን እያስጣለ። እድል በኔ ጨከነ ስል-በምረት እጅ ደባበሰኝ አንቺ ነጥቆ ከቅፌ ላይ-በትውስታ ደሞ ካሰኝ። አሰታወሰኝ አስታወሰኝ። ወድያው ታይቶ :ጠፊ ኩርፍያሽ ገራም ሳቅሽ : ልዝብ ልፍያሽ ያለም ዘፋኝ የማያውቀውማንበብ ይቀጥሉ…

ግርምሽ ሲታወሱ

ግርማ ወልደጊዮርጊስ ፕሬዚዳንት ሁኑው የተመረጡ እለት ብዙ ሰዎች ተገርመዋል ። ከእስክንድር ነጋ ጋዜጦች አንዱ ዜናውን የዘገበችው ” ወያኔ አበደች ” በሚል ርእስ እንደነበር ትዝ ይለኛል። አንድ አሙስ የቀረው ሽማግሌ እንዴት ለዚህ ሚና ይታጫል በሚል እብሪት የተቹ አልጠፉም ። ብዙዎቻችን “ሽማግሌማንበብ ይቀጥሉ…

ጉደኛ ስንኞች

እንዳለመታደል ሁኖ የጎጃሙ ጌታ የራስ አዳል ልጆች አሪፍ ያገር አስተዳዳሪ አልነበሩም። እንደመታደል ሆኖ ደሞ የተዋጣላቸው ባለቅኔዎች ነበሩ። ግጥሞቻቸው ከኑሯችን ጋር በጣም የተቆራኙ ናቸው። ለምሳሌ የግፍ ዘገባ በሰማን ቁጥር የምንቀባበለው። “የለህም እንዳልል ይመሻል ይነጋል አለህም እንዳልል እንዲህ ይደረጋል” የሚለውን ገራሚ ግጥምማንበብ ይቀጥሉ…

ሁሉም ለምን ያልፋል?

የጣፈንታ መዳፍ ደስታና መከራን: እያፈሰ ሲናኝ “ሁሉም ያልፋል ” ብሎ : ማነው የሚያፅናናኝ? ግራ በተጋባ :በዞረበት አገር ካንቺ የምጋራው :ሰናይ ሰናይ ነገር ፊቴን የሚያበራው :ያይንሽ ላይ ወጋገን ዛሬ ተለኩሶ : የሚያሳየኝ ነገን ለምን ሲባል ይለፍ : ያንን መሳይ ፍቅር ደሰታሽማንበብ ይቀጥሉ…

ትናንት ዛሬ አደለም

ይገርማል!! ያገራችን ገበሬ የሚያርስበት በሬና ማረሻ ጥንታዊ ሰው ከአራት ሺህ አመት በፊት ይገለገልበት የነበረውን ነው። ይሁን እንጂ ቢቀናው ክላሺንኮቭ ይታጠቃል። ደሞ ገበሬውን ዘመናዊ ጠመንጃ እንጂ ዘመናዊ ማረሻ ለማስታጠቅ የሚያልም አክቲቪስት አይተን አናውቅም። ዘመናይ የብሄር አክትቪስት ጦርነት በናፈቀ ቁጥር ያባቶቹን ጀብድማንበብ ይቀጥሉ…

ተማሪዎችን እንረዳቸው!

  የዩንቨርስቴ ተማሪዎች ወገን ለይተው በተደባደቡ ቁጥር ምን አደባደባቸው ብሎ የሚጠይቅ የለም። ከዚያ ይልቅ መስደብ መሸርደድ ማዋረድና ሙድ መያዝ ለምደናል። ባገራችን ከቤተመቅደስ እስከ ስቴድየም ድረስ ጎሰኝነት ያልነካካው ተቁዋም እንደለሌ እናውቃለን። ተማሪዎች ከሌላው የከተማ ነዋሪ የከፋ ጎሰኝነት እንደተሸከሙ የምናረጋግጥበት ሚዛን የለም።ማንበብ ይቀጥሉ…

ጐጆ ቤት

ሀገርስ ጐጆ ናት !!! መሪዋም ምሰሶ ሹማምንቷም ማገር  አንዳንዶቹም ቋሚ ሌሎቹም ወጋግራ ሰራዊቷም አጥር! ሀገርስ ጐጆ ናት !!! ሕዝቡም ክዳን ሆኖ ጐጆውን አልብሶ እንደሳር ቢቀጥን፤ ቢኖር ተራ መስሎ ከዝናብ ያድናል፤ ውርጩን አሰናብቶ ፀሃይን ይከላል፤ በጥላው ከልሎ… ሀገርስ ጐጆ ናት !!!ማንበብ ይቀጥሉ…

በኅዳር ውስጥ እኔን

(የነፍሴ ክስ) ተወው! ቆሻሻህን ተወው  ከሳቱ ዳር እራቅ ጭለማን ልበሰው ጥቁር ካባ ደርብ ዓይንህ ይጨልመው። … ግዴለህም ተወው እቤትህ ግባና ዓይንህን ጨፍነህ ስላሳመምካቸው ስላቆሰልካቸው ነፍሳት አስብና ራስህን ክሰስ ራስህን ውቀስ ራስህን አጥን ተረማመድበት በንፁሀን ፋና። … የነፍስህን እድፍ የውስጥህን ጉድፍማንበብ ይቀጥሉ…

ኖረሽ እይው በቃ

(ለoptimistቶች) ጨለማ ነህ ብለሽ እኔን ስትተቺ ዘልለሽ አትጠግቢ ስቀሽ አትሰለቺ ወርሃ- ፅጌ ነው አመት ሙሉ ላንቺ። ደሞ በየቀኑ ፋሲካ ነው ኑሮሽ ያለም ሰቀቀኑ ሩቅ ነው ለጆሮሽ (የፍጥረት ሰቆቃ) ለጋ ነው አእምሮሽ ገላሽም ነው ጮርቃ ሌላም አልልሽም ኖረሽ እይው በቃ። በየጎዳናሽማንበብ ይቀጥሉ…