የዚህ ትውልድ አባል ነኝ!

በመውደድ ወይ በመጥላት አልፍቀውም። ያለፈው ትውልድ ውላጅ ነኝ። የመጪው ትውልድ ወላጅ ነኝ። ያለፈው ትውልድ “አዬ ልጅ” እያለ ያሾፍብኛል፤ መጪው ትውልድ ይኮርጅኛል( ወደፊት “አይ አባት” ብሎ ይስቅብኝ ይሆናል -ግድ አይሰጠኝም) ለሁሉ ፈጣን ነኝ። ሁሉን በፍጥነት አይቼ በፍጥነት አልፋለሁ። ችክ ማለት አልወድም።ማንበብ ይቀጥሉ…

መረቅ

(ስሜቴን ለመግለፅ እንጂ፣ እንዳይንዛዛ( እንዳልንዛዛ) ሁለት ወይ ሶስት ጊዜ ቆራርጬ ለመፖሰት እገደዳለሁ) ክብነት(ሙሉዕነት) በመረቅ የመፅሓፉ ሀይለኛ ጉልበት እዚህ ጋር አለ።አዳም የህይወትን ክብነት ለማሳየት ገፀባህሪያቱንና ታሪክን በመጠቀም እንጀራውን ይጋግራል። ሀ. በገፀባህሪቱ፡― መፅሐፉ አራት ዋና ገፀባህሪያት አሉት።አራት(ምናልባትም “ዐራት”) የምልዑነት መገለጫ ነው። በማንበብ ይቀጥሉ…

የሁለት እህትማማቾች ወግ

የዛሬ ወር ተኩል ገደማ ለሳምንታት ቆይታ ወደ አሜሪካ ሄጄ ነበር፡፡ የጉዞ ሃሳቤን የሰሙ እዚህም አዚያም ያሉ ዘመድና ወዳጆቼ እኔ ‹‹ልዋጭ ልዋጭ›› የምለውን የእቃ ውሰጂና አምጪልን ጥያቄያቸውን ጀመሩ፡፡ በርበሬና ሽሮን በጋላክሲ ስልክና በሌቫይስ ጅንስ የመለወጥ ጥያቄ፡፡ ቡላና ኮሰረትን በናይኪ ስኒከርና በሬይባንማንበብ ይቀጥሉ…

በመጨረሻም…

በመጨረሻም ራሴን ላጠፋ ነው። ቃሉ ራሱ ደስ ሲል! ራስን ማጥፋት!! ፓለቲከኞች “የራስን ዕድል በራስ መወሰን ” እንደሚሉት ነው። ከህይወት ምን ቀረኝ? ምንም! አንድ የቀረኝ ነገር ራሴን የማጥፋት ድርጊት ብቻ ነው። ከዛ በኋላ ሀገሬ ሞት ነው። ከሞት ግድግዳ ወዲህ ምንም የሚጎትተኝማንበብ ይቀጥሉ…

ላንቺ ግጥም እየፃፍኩ ነበር!

የሆነ የዓለም ጥግ ላይ ህፃናት በረሃብ ሲያልቁ እኔ ላንቺ ግጥም እየፃፍኩ ነበር። ሁሉም ሲያድጉ አንቺን ማግኘት እንደማይችሉ ስለገባችው እንደሚያለቅሱ ይሰማኝ ነበር። እንደዚህ እያሰብኩ ግጥም እየፃፍኩልሽ ነበር። ፈጣሪ ዓለም የሚያጠፋት በቁጣ ነው ሲሉኝ እገረማለሁ። ፈጣሪ ዓለምን ካጠፋ አንቺ ስትሞቺ በሚደርስበት ሀዘንማንበብ ይቀጥሉ…

ይሰለቻል

በመጀመሪያ እግዜር ብቻውን ነበር። ብቸኝ ት ሰለቸው። ብቸኝነት ሰለቸውና ዓለምን ፈጠረ። የፈጠረውን አይቶ ደስ አላለውም፣ ሰለቸው እንጂ። የሰለቸውን ዓለም ትቶ ሌላ አዲስ ነገር ፍለጋ ሄደ። ዓለምም ከዛን ወዲህ መሰልቸት ወለል ላይ ሆና የአምላኳን መምጣት በጥፍሯ ቆማ ትጠብቃለች። እኔ የዓለም አካልማንበብ ይቀጥሉ…

ባትሄጂ ኖሮ…!

ባትሄጂ ኖሮ፣ ብትሆኝ ከኔ እቅፍ እዚህ ከፃፍኩት ላይ፣አንድም መስመር አልፅፍ፡፡ አቤት ባትሄጂ! ግን አንቺ አልቆምሽም መጓዝ አልደከምሽም፡፡ ይሄዋ፡- ከሄድሽ በኋላ ዐይኔም አይታየው፣ ጆሮዬም አይሰማ ልቤም ደም የሚረጭ፣ ባንቺ ስለደማ፡፡ አንቺ በመሄድሽ፤ ያለህይወት በህይወት ተነጥላኝ ነብሴ፣ ያው አለሁ ሙት ሆኜ፣ ለሰዉምማንበብ ይቀጥሉ…

ቤት ሰራሽ ጦርነት

በአንዲት ሀገር ላይ ጨለማና ብርሃን ክፉኛ ተጣሉ አሸናፊ እስኪለይ ድብድብ ቀጠሉ የጨለማን ግንባር-አናቱን ሊበሳ ብርሃን ይጥራል የጨረራ መዓት ጨለማን ለመምታት ተግቶ ይወረውራል እውሩ ጨለማ መርግ መርግ ፅልመት ከአካሉ ያነሳል ድቅድቅ አሰልፎ ብርሃን ላይ ያፈሳል ተው ባይ በሌለበት ሃይ ባይ በጠፋበትማንበብ ይቀጥሉ…

የተደገሙ ወላጆች!

(ልጆቻችሁ፣ ልጆቻችሁ አይደሉም?) ካህሊል ጅብራን “The Prophet” በተባለ ስራው “ስለ ልጆች ንገረን” ለሚል ጥያቄ በነብዩ አንደበት ይናገራል። “your children are not your children” ምን? ልጆቻችሁ ልጆቻችሁ አይደሉም? እና የኛ ካልሆኑ የማን ናቸው? ነው ወላጆቻችን ናቸው? አትቀልዳ ካህሊል። እስቲ ትንሽ አብራራው።ማንበብ ይቀጥሉ…

ፈሪ ነኝ!

ፈሪ ነኝ! ሞዴል ፈርቶ አደር! ውሃ ውስጥ ሆኜ የሚያልበኝ። በርግጥ ውሃው “ፍል ውሃ” ከሆነ ማንም ሊያልበው ይችላል። እኔ ግን አጥንት በሚቆረጥም ውሃ ውስጥም ያልበኛል። መፅሀፉ፣ “የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው” ይላል። እኔ ግን “የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ፣ መጨረሻውም ሁሉንም መፍራትማንበብ ይቀጥሉ…