አንድ ጨለምኛ ግጥም፣ ለአንዲት ጨለምተኛ ሀገር

*** አንቺ ሃሳበ ብዙ፣ አንቺ ጓዘ ብዙ አቅም የሚፈትን፣ጉልበት የሚያጣምን ከህይወት ዋጋ ይልቅ በሞት ከሚያሳምን ከዚህ ትግል ጉዞ የሚገላግሉ- ልጆችሽ እያሉ የት እንዲያደርስሽ ነው ሰርክ መባተሉ? “ሁሉ ነፃ አይደለም፣ ውደቁ ተነሱ ቆፍሩ አፈር ማሱ” የሚሉ ቂሎችን ከጆሮሽ አርቂ ለማይረባ ነገርማንበብ ይቀጥሉ…

ማነሽ ?!

ከእለታት በአንዱ፣ በቅዱስ እርጉም ቀን መንገድ ያገናኘን ድንገት የተያየን አንቺ አልፈሽኝ ስትሄጅ፣ እዛው ያስቀረሽኝ! …ላይሽን ሸፍኖት ጥቁር ጨለማ ጨርቅ ዐይንሽን ብቻ እንጂ፣ ሌላሽን የማላውቅ ማነሽ አንቺዬዋ? ማንነትሽ ማነው? አቅል እያሳተ፣ መንገድ የሚያስቀረው? ወንድን እንዳታስት ትጀቦን፣ ትሸፈን-ይሉትን የሰማሽ አይታይ አካልሽ ውዴማንበብ ይቀጥሉ…

“ከገዳይ ጋር ፍቅር”

አይጥ የድመቱ ነገር ግራ ገብቷታል። በተደጋጋሚ ፍቅሯን ልታሳየው ብትሞክርም ሊገባው አልቻለም። ከጉድጓዷ ስትወጣ አምራ እና ተኳኩላ ትወጣች። ድመቱ እንደ ሁል ጊዜ ከጉድጓዷ ፊት ለፊት ሆኖ ታገኘዋለች። አማላይ እንቅስቃሴ ልታሳየው ትሞክራለች። በፍቅር ዓይን ታየዋለች። እሱ ፍንክች የለም። እንዲህ መውደዷን ልታሳየው እየሞከረችም፣ማንበብ ይቀጥሉ…

የሕዝብ ችኩል ምን ይነክሳል?

…… ወሩን ሳስበው ፆም ነው፡፡ፆም ስለሆነ፣ አንድ ሆቴል ገብቼ ቅቅል በላሁ፡፡ …..ቅቅል የበላሁት ስላማረኝ ብቻ አይደለም የበላሁት፣ ፆም ስለሆነም ነው፡፡ ብዙዎች ከሚያደርጉት በተቃራኒ ማድረግ ደስ ስለሚለኝ ነው፡፡ ለነገሩ እውነቱን እናውራ ከተባለ፣ ቅቅል አልበላሁም፡፡ በዚህ ቅቅል ኑሮ፣ ቅቅል መብላት እራስን መቀቀልማንበብ ይቀጥሉ…

ማሞና ማሚቱ

<<ማሞና ማሚቱ በሉ ዳቦ ቆሎ ሮጡ ወደቁ ተነሱ በቶሎ>> /ቃላዊ ግጥም/ ማሞና ማሚቱ፣ ጠኔ እየጣላቸው፣ ነብስ የሚያነሳቸው ሌሎች እኮ አይደሉም፣ እኔና አንተ ናቸው፡፡ ቶሎ እየወደቅን ቶሎ የምንነሳ ቀለባችን ቆሎ ኑሯችን አበሳ ማሞና ማሚቱ፣ እኛ ነን አትርሳ፡፡ ከህይወት ግብግብ፣ እየሮጡ ገብተውማንበብ ይቀጥሉ…

ህዳሴው የማይነካቸው፣ ህዳሴውን የማይነኩ የሰፈሬ ወጣቶች

አንዳንዴ በግድ መገረብ ያለባቸው ፖስቶች አሉ ብለው እናምናለን። አምነንም እንገርባለን… ******* ህዳሴው የማይነካቸው፣ ህዳሴውን የማይነኩ የሰፈሬ ወጣቶች (ይሄ ፓስት ህዳሴው ትክክለኛ ነው፣ አይደለም ብሎ አይነታረክም) ‹‹‹‹‹‹ ››››››› እዚህች ሰፈር ነው ያደኩት፡፡ አድጌ “እግሬን ከመፍታቴ” በፊት ዓለም ከዚህች ሰፈር አትበልጥም ነበርማንበብ ይቀጥሉ…

ዝፍታ

(ከከፍታ እና ከዝቅታ የተዳቀለ) ****** ከዝቅታ አንስተን ከፍታ መንበር ላይ የሾምነው በሙሉ ተንከባሎ መውደቅ ሆነብን አመሉ እዚህ ዝቅታ ላይ አብሮን የቆሸሸ፣ አብሮን የጠለሸ አጣጥበን ብንሾመው ምነው ባንዴ ሸሸ? ዝቅ ለለመደ ከፍታ ይከብዳል? ብርድ ለለመደ ወበቁ ይበርዳል? ሰው ባፈጣጠሩ ዝቅታ ይወዳል?ማንበብ ይቀጥሉ…

ጎሬ-ቤቶች!

(ፀሀፊው፣ እኔ) ***** ጎረቤታሞች ናቸው፡፡ ከአጠራቸው ውጪ ግን ምናቸውም አይገናኝም። የአንዷ ኑሮ ቅንጦት የሌላኛዋ እጦት ነው፡፡ ያችኛዋ የምትበላው የላትም። ይህችኛዋ የማትበላው የላትም። አንድ ቀን… ያቺ የድህነት አቅም ማሳያዋ ሴት….ወሰነች! “የምበላው አጥቼ፣ ገርጥቼ ነጥቼ ከምሞት… አንድ ቀን እንኳን ጀመበር እስክትጠልቅ አጊጬ፣ተውቤማንበብ ይቀጥሉ…

ለቃልህ ታምኜ…

በአንዲት እርጉም ቀን ልቤ ፅድቅ ሻተ; ከመፅሐፍህ መሃል “ግራህን ቢመቱ ቀኝ ስጥ” የሚል ቃል ለነብሴ ሸተተ; እልፍ ጠላቶቼ መንገዴን ተረዱ; በእፀድቃለሁ ሰበብ መስከኔን ወደዱ ; መጡ ተሰልፈው:- ግራዬን ነገሉ; ከቀኙም አንድ አሉ ወገሩኝ ደጋግመው ክንዳቸው እስኪዝል; ሁሉን ዝም አልክዋቸው ፅድቅህማንበብ ይቀጥሉ…

አንበሳ ዙሪያችን ሚዳቅዋ ልባችን!

አንበሳ ዙሪያችን ሚዳቅዋ ልባችን! (የአንበሳ ልብ ቢጠፋ፣ በአንበሳ ጫማ ሮጦ የማምለጥ ሀገራዊ ጥበብ) ********* እስቲ ዙሪያችሁን ተመልከቱት? ሁሉ ነገር አንበሳ ነው!! ተረታችን ሲጀምር፣ “አንድ አንበሳ ነበረ…” ብሎ ነው፡፡ አውቶብሳችን አንበሳ ነው፡፡ ጫማችን አንበሳ ነው፡፡ ዘፈናችን “ቀነኒሳ አንበሳ”፣ “አንበሳው አገሳ” …ማንበብ ይቀጥሉ…