የሆነ ጊዜ ላይ አንዲት ቆንጅየ ልጅ ፍሬንድ ሪኩየስት ላከችልኝ! በእህትነት ተቀበልኳት ! ትንሽ ቆይቼ እህትነቱን ባንድ እርምጃ ላሳድገው ብየ በማሰብ በኢንቦክስ “ ሰፈርሽ የት ነው? አላማስ አለሽ? ” ምናምን ማለት ጀመርሁ ፤ ጥቂት እንዳወጋሁት ግን በሴት ፎቶ የተጠለለ ወንድ መሆኑንማንበብ ይቀጥሉ…
ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ (ክፍል ሰባት)
“አልቻልኩም። …. አልቻልኩም!” ሁለት እጆችዋን ጨብጣ ደረቴን እየደበደበች ታለቅሳለች። ጉንጮቿ እና ከንፈርዋ ይንቀጠቀጣሉ። አንጀት የራቀው ሆድዋ ይርበተበታል። እየደጋገምኩ “እሺ” ከማለት ውጪ የምለው አጣሁ። ድብደባዋን ስታበቃ ንፁህ ያልሆነው መሬት ላይ በነጭ ሱሪዋ ተቀመጠች። “ላናግርህ እፈልጋለሁ” ብላ ሱቋ ጠርታኝ ነው ሱቁን ዘግታማንበብ ይቀጥሉ…
ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ… (ክፍል ስድስት)
“እስክትወስን እጠብቃታለሁ።” ይለኛል። ሁሌም የምንገናኝበት ቦታችን ‘የምናውራው አለ’ ብሎኝ ተገናኝተኝ የጀበና ቡናችንን እየጠጣን። “እኔስ? በፍቅርህ የነሆለለ ጅል ልቤስ? ምን ላድርገው? እስከመቼ ጠብቅ ልበለው? ከሚስቱ እስኪታረቅ ልበለው እስኪለያይ? ንገረኝ የቱን ነው የምጠብቀው?” እንባዬ የአይኔን ድንበር አልፎ ተንዠቀዠቀ። ይሄን ያልኩት ብዙ ስለሷማንበብ ይቀጥሉ…
ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ… (ክፍል አምስት)
“እናውራ? ማውራት አለብን!” አለኝ አምስት ለሊቶች ሳይነካካኝ አቅፎኝ ካደረ በኋላ። አምስት ጠዋቶች ከንፈሬን ሳይስመኝ ደህና ዋዪ ካለኝ በኋላ። አምስት አመሻሾች ደረቱ ላይ አቅፎ ግንባሬን ሳይስመኝ እንዴት ዋልሽ ካለኝ በኋላ…. “Finally” አልኩኝ ይህን እንዲለኝ ስጠብቅ እንደነበር በደንብ እያሳበቅኩ “እንዴ? እንድናወራ እየጠበቅሽማንበብ ይቀጥሉ…
ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ… (ክፍል አራት)
ባሌን እንዲህ እፍፍፍ ያስደረገችውን ሴት ለማየት “የተለመደ” ቦታቸው ባሌን ተከተልኩት። ከስራ እኔን እቤት ካደረሰ በኋላ ነው የወጣው። የጀበኛ ቡና የሚሸጥበት ቤት? ይሄ ነው የተለመደ ቦታቸው? መኪናውን አቁሞ ወረደ። ታክሲውን አስቁሜ በዓይኔ ተከተልኩት። ከተቃራኒ አቅጣጫ እየመጣች ከነበረች ሴት ጋር በፈገግታ ተጠባበቁ።ማንበብ ይቀጥሉ…
እንደሱ አይደለም
የምወዳቸውን ዘፈኖች ወደ ሙዚቃ ቪድዮ መቀየራቸውን ስሰማ ለማየት ፈራ ተባ እላለሁ ፤ በጣም የወደድኩትን ዘፈን በካሜራ አጉል ተርጉመው ሲያበላሹብኝ ይነደኛል ፤ በራሴም ደርሶብኛል ፤ ከጥቂት አመታት በፊት ነፍሱን ይማርና ኤልያስ መልካ አንድ ዜማ ሰደደልኝ፤ “ ዝምታየ” የሚል ግጥም አለበስኩና መልሼማንበብ ይቀጥሉ…
ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ… (ክፍል ሦስት)
“ልጅ ልሰጥሽ ስለማልችል ትተይኛለሽ?” አለኝ “ስንጋባም መውለድ እንደማትችል ታውቅ ነበር?” “አዎ ” “ለምን አልነገርከኝም?” “እንዳላጣሽ ፈርቼ። ብነግርሽ ኖሮ ታገቢኝ ነበር?” “ምርጫ አልሰጠኸኝምኮ! ከልጄና ከፍቅርህ እንድመርጥ ምርጫ አልሰጠኸኝም! ራስህን ራስህ መረጥክልኝ!! ” “እኔ ብሆን ልጅ አልሰጠሽኝም ብዬ አልተውሽም! ይሄን የሚሻገር ፍቅርማንበብ ይቀጥሉ…
ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ… (ክፍል ሁለት)
ሰይጣን ይሁን ራሴ ወይም ፈጣሪ ለሀጥያት በቀጠሩልኝ ቀን ከአለቃዬ ጋር ባለግኩ። ይኸው ነው ሀጥያቴ! ጨው የሌለው አልጫ ወጥ አልጫ ወጥ የሚል ትዳር ውስጥ ፀጥ ለጥ ብዬ እንድቆይ ባለእዳ ያደረገኝ ሀጥያቴ ይኸው ነው!! ይኸው ነው ብዬ አቀለልኩት? ካልጠፋ ቀን የዛን ቀንማንበብ ይቀጥሉ…
ቅጥቅጥ! በላባ ትራስ!
ብልፅግና ፓርቲን ለመደገፍ በተካሄደው ሰልፍ ላይ ወዳጄ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ሲወገዝ አይቸ ገረመኝ ! ብልጥግናን እንደግፋለን ዳንኤል ክብረትን እናወግዛለን ማለትኮ “ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እንሞታለን በረኛውን ግን እንገድለዋለን “ እንደማለት ነው ፤ ዳኒ አንደበቱ የማይደነቃቀፍ ተናጋሪ ብእሩም የማይደክም ፀሀፊ ነው፤ማንበብ ይቀጥሉ…
ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ እጅጉን ደስ አለኝ!! (ክፍል አንድ)
“ቦታችን በተለመደው ሰዓት እጠብቅሃለሁ። አፈቅርሃለሁ!” የሚል መልዕክት ነው እንዲህ ያስቦረቀኝ!! እሱ ጏዳ ቁርስ እያበሰለ የሚያማስለው የመጥበሻ ድምፅ ይሰማኛል። ስልኩ መልእክት ሲቀበል ድምፅ አሰማ ያለወትሮዬ እጅ ጥሎኝ ስልኩን አነሳሁት። አንደኛ የራሳቸው ቦታ አላቸው! እኔና እሱ የኛ የምንለው ቦታ ኖሮን አያውቅም!! ከቤታችንማንበብ ይቀጥሉ…