እኔና አንቺ

“አንተ ሴሰኛ አይደለህም።” ትዪኛለሽ። ሴሰኝነት ‘ስሜ’ መሆኑን አንቺም፣ እኔም፣ ከጎኔ የሚሻጡት ሴቶችም፣ እኔን የሚያውቁኝም ሁሉ እናውቃለን። ለራሴ ‘ያለማወቅሽን እና የዋህነትሽን’ ነገርኩት። ላንቺ ግን ዓይኖቼንም ልቤንም የጠለፈውን ህልም የመሰለ ውበት ያለው አካልሽን እያየሁ ጥርሴን ለመግለጥ ከንፈሬን አሸሸሁልሽ …….. ሚስጥር አዘል ወጋገንማንበብ ይቀጥሉ…

የገቢዎች ነገር እና 40/60

በጥዋት አልጋዬ ውስጥ ሆኜ እየተብሰከሰኩ ነው። የቤት ኪራይ መክፈያዬ ደርሷል……ኤዲያ! ” መቼ ነው ግን የራሴ ቤት የሚኖረኝ?” ።ትላንት በጉጉት ስጠብቀው የነበረው የ40/60 እጣ እንደወጣ በዜና አይቻለሁ…እጣ ውስጥ የተካተቱት መጀመሪያውኑም መቶ ፐርሰንት የከፈሉ ብቻ እንደሆነም ተነግሯል……የወጣው እጣ አንድ ሺ እንኳን አይሞላም።ማንበብ ይቀጥሉ…

ካልፎሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ

(ታሪካዊ ልቦለድ) To be honest with you ሲያትል በተደረገው የዲያስፖራ የግርኳስ ውድድር ወደ ሚደረበት ስቴዲየም የሄድኩት ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ጋር ሳልነካካ መፅሃፌን ሸጬ አገሬ ለመግባት ነበር፤ (ከመፅሃፍ ሻጭ የሚገኘው ገቢ አስር በመቶ ለእኔ ሲሆን ፤ ቀሪው ለቤት አከራየ ለጋሽ ጣሰውማንበብ ይቀጥሉ…

“ያ’ባ ምናሴ ፍትህ”

በአንዲት “ሊቃውንት” በሚበዙባት ደብር ውስጥ የኒህ የሁለቱ ሊቃውንት ፀብ ለያዥ ለገናዥ አስቸጋሪ ሆነ። በቃላት ምልልስ የጀመረው የመሪጌታ ቀፀላ ኤፍሬም እና የቀኝጌታ በፍርዱ ሄኖክ ፀብ፤ እጅጉን ብሶበት በምዕመናኑ ፊት ከዓውደ ምህረቱ ስር ለድብድብ ተጋበዙ። በቅርብ የተገኙት፤ ከቅዳሴ የወጡት ቆራቢ ምዕመናን ገላግለው፤ማንበብ ይቀጥሉ…

ስለ ፍቅር ሲባል!

<በዘመኑ በመፈጠሬ እኮራለሁ> ብል ታበይክ እሚለኝ እሱ ማነው?ፍቅር እና ትዕቢት ባንድ መንበር አብረው እንዳይቆሙ እናውቃለንና። ዳሩ ግን ሰውየው በፊደል ቆጠራ የልጅነት ዘመኔ አቡጊዳ ብሎ በዜማ ሀሁ እንደለከፈኝ አለ።ነፍስ ባላወቀ ቦላሌ ባላንጠለጠለ የልጅነት ዘመናችን ነፍሷ በሰማይ ካለ አብሮ አደጌ ካዲሴ እናማንበብ ይቀጥሉ…

መማርና መማር

(ሲጠብቅና ሲላላ) ትዳርን የተቃናና የተሳካ ለማድረግ በሁለት ባላዎች ላይ መትከል ያሻል ይላሉ ሊቃውንቱ። በመማርና በመማር። ሰው ሌላውን ሥራ ሁሉ የሚሠራው አንድም ተምሮ አንድም ለምዶ ነው። ትዳር ሲመሠርት ግን ትምህርትም ልምድም የለም። ትዳርን እንደ ትምህርት ዓይነት መርጦ፣ ከፊደል እስከ ዳዊት ደግሞ፤ማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹ገዳዬ…ገዳዬ…››

(መነሻ ሃሳብ፤ የሞፋሳ (ኬንያዊ ገጣሚ) ‹‹ልጅቷ›› ግጥም) ፀሐያቸው ጠልቃ በሰው ሀገር መሽቶብኝ ነበር። ጨልሟል። የተለመደውን አውቶብሴን ተሳፈርኩ። አዲስ ነገር የለውም። ሁሌም የምጠብቀው፣ ሁሌም በጠበቅኩት ሰአት የሚመጣው የማይዛነፍ የእለት ውሎዬን የሚደመድመው አውቶብስ ነው። እንደተቀመጥኩ፣ ሰንደቅ የሚያሰቅል ቁመት ያለው ውብም፣ ሎጋም ኢትዮጵያዊማንበብ ይቀጥሉ…

እንግዶቹ

“… ዓይን ወረተኛ ነው ያመጣል እንግዳ’’ የሚል ስንኝ ያለበት የባላገር ዘፈን አውቃለሁ፤ በርግጥ ዘፈኑ እንደሚነግረን ዓይን ብቻ አይደለም አዲስ ለምዶ እንግዳ ይዞ የሚመጣው፤ ጆሮም፣ ልብም፣ እጅም፣ እግርም መጠናቸው ይለያይ እንደሆነ ነው እንጂ፣ ከአዲስ ነገር ጋር አስተዋውቀውንና አላምደውን እንግዳ ይዘውብን ይመጣሉ።ማንበብ ይቀጥሉ…

ካልፎ ሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ

(ትራጄዲ ትረካ) ሰሞኑን የወንድሙ ጂራን ዘፈን የምገርበው ያለ ምክንያት አይደለም። ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ ካልሲየን ፍለጋ በየጥጉ እሰማራለሁ። የቀኝ ካልሲየ ምስኪን ናት። እንደ ገራም የድመት ግልገል ከመመገቢያው ጠረጴዛ እግር ስር ኩርትም ብላ ትገኛለች። የግራ ካልሲየን ግን እፀ -መሰውር የረገጥሁባት ይመስል ደብዛዋማንበብ ይቀጥሉ…

ጋሹ እንዴት እንደተሰደደ?

  የዚች ጨዋታ መነሻ የሆነኝ የዛሬ ምናምን አመት ያነብኩት “ያረብ ሌሊቶች ” ተረት ነው። ጋሹ ታታሪና አይናፋር ባላገር ነው። ሲኖር ሲኖር; በስንት መከራ አንዲት ቆንጆ አጭቶ አገባ። የሰርጉ ቀን ተበልቶ ተጠጥቶ ጭፈራው ደራ። ሚዜዎችና አጃቢዎች ሙሽሮች እንዲጨፍሩ ጋበዙዋቸው። ጋሹ ግብዣውንማንበብ ይቀጥሉ…