ኢትዮጵያ በአማልክት እና በተከታዮቻቸው ዓይን

“… እናቴ ሆይ በዚህች በምባርካት አገር በኢትዮጵያ የሚኖሩ ሰዎችን እስከ ዓለም መጨረሻ ድረስ አሥራት ይሆኑሽ ዘንድ ሰጥቼሻለሁ። እናቴ ሆይ አሁንም ወደዚያች አገር እንሄድ ዘንድ ተነሺ። ደሴቶችና የተቀደሱ፣ ወንዞችዋ ያማሩ፣ ውሃዎችዋ የጠሩ፣ ዛፎችዋና ተራራዎችዋ የተዋቡ ናቸውና አሳይሻለሁ አለኝ።” ይላል አንብር መስቀልየማንበብ ይቀጥሉ…

እርዳታ እና እኔ

ግኑኝነታችን የሚጀምረው፣ በልጅነቴ ከበላሁት የእርዳታ “ፋፋ” እና “ዘይት” ነው። የሆነ ጊዜ ወተትም ነበር። የሆድ በሽታ ለቀቀብኝና ለሳምንታት ላይና ታይ በሌ ስል ኖሬ ይቺን ዓለም በጨቅላነት ሳልገላገላት ለትንሽ አመለጥኩ። ኑሮን በድህነት ስትገፋ በወር የሚሰጥህ 5 እና 10 ኪሎግራም ምጽወታ ነፍስህን ለማቆየትማንበብ ይቀጥሉ…

የጎረቤት ወግ

  ወደቤቴ ከመግባቴ በፊት ከጨዋ ሚኒ ማርኬት ሁለት ኪሎ ማንጎ ገዛሁ፤ “በጥቁር ፌስታል አርጊልኝ” አልኩዋት ማሾን(ማሾ የሚኒ ማርኬቱ ባለቤት ናት) “አንተ ደሞ የጥቁር ፌስታል ልክፍት አለብህ “አለችኝ እየሳቀች። ውነቷን ነው! ከፍራፍሬው ጥራት በማይተናነስ መጠን የፌስታሉ ቀለም ያሳስበኛል፤ ጥቁር ፌስታል በውስጡማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹አላቅሱኝ››

ትላንት አባቴ ሞተ። ካሁን በኋላ በለመድናት ሰአት የውጪ በራችንን በቁልፉ ‹‹ቃ›› አድርጎ ከፍቶ ላይገባ፣ ካሁን በኋላ ሳመሽ በረንዳ ላይ ጋቢውን ለብሶ እሳት ጎርሶ ጠብቆ ላይቆጣኝ፣ ካሁን በኋላ የአመት በአል ድፎ እየሳቀ ላይቆርስ፣ ካሁን በኋላ ልጄን፣ የልጅ ልጁን አቅፎ ላይስም… ሞተ።ማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹የሪል እስቴት ማላገጫዎች››

አሁንስ እነዚህ ኑሮ እጅ በጆሮ ያስያዘው ምስኪን ሕዝብ ላይ በይፋ የሚያላግጡ የሪል እስቴት ማስታወቂያዎች ቃር ሆኑብኝ። አነፈሩኝ። መቼስ፣ በለስ ቀንቶት፣ ወርሶ ወይም ከመንግሥቱ ነዋይ ግርግር ጀምሮ ቆጥቦ እዚህ ለደረሰ የናጠጠ ሃብታም ማስተዋወቃቸውን አልቃወምም። እነዚህ በሌላ የተንጣለለ እልፍኛቸው እየኖሩ ማስታወቂያውን የሚመለከቱማንበብ ይቀጥሉ…

ዘውድም እነሱ ጎፈርም እነሱ

ቀምጣላ ስድስተኛ ቤቷን በአዲስ አበባ የገዛችው ዘመን ያገነነናት ሙሰኛ የድሮ የትምህርት ቤት ጓደኛዬን ካገኘሁ ወዲህ የአርባ-ስልሳ ነገር ያነደኝ፣ የኮንዶሚኒየም ኪራይ ያንጨረጭረኝ ጀምሯል። ልጅቱ አንድ ኮንዶሚኒየም፣ አንድ የሰንሻይን ሪል ሰቴት አፓርትማ፣ አንድ የፍሊንትስቶን ሆምስ ታወን ሃውስ፣ አንድ የማህበር ቤት፣ አንድ ሰበታማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹ኑ! አንድ ቤት ግቡ!››

መስሪያ ቤቴ ሁለት የከፍተኛ መደብ ልጆች ብቻ የሚማሩባቸው ትምህርት ቤቶች መሃከል የተሰነገ ነው። ጠዋት ሲገቡ፣ እረፍት ሲወጡ፣ ማታ ሲሄዱ አያቸዋለሁ። ከወዛቸው፣ ከቀብራራነታቸው፣ አማርኛን ከደቆሰው እንግሊዝኛቸው ጎልቶ የሚታየኝ፤ መጀመሪያ የሚቀበለኝ ዘወትር ዳንኪራ የሚረግጡበት አደንቋሪ፣ ተንጫራሪ ራፕ ሙዚቃቸው ነው። የነ ድሬክ፣ የነማንበብ ይቀጥሉ…

የጸሎተ ሐሙስ ንፍሮ ( ጉልባን)

ጉልባን ከተፈተገ ሰንዴ ከባቄላና ከሽምብራ ጋር ተቀቅሎ የሚዘጋጅ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ በእለተ ሐሙስ የፀሎት ቀን ወደ ስቅለተ አርብ ለመሸጋገሪያ በምዕመናን የሚቀመስ መንፈሳዊ ቁርስ ነው። ታሪኩን ለማስጠር ያህል ነው እንጂ ይህ ቁርስ ጥንት እስራዔላውያን ከግብጽ ባረነት ወጥተው የቀይባህርን ከተሻገሩበት ረጅምማንበብ ይቀጥሉ…

ሻረው፣ እንዴት እንዳመለጠ?!

ባለፈው ፣ተጠባባቂ ፓስተር ገመቹ ቸርች ካልወሰድኩህ ሞቸ እገኛለሁ አለኝ፤ “በውቄ እግዜርን ፍለጋ ላይ ነኝ ትል የለ?! ታድያ እግዜርን የምትፈልገው ረከቦት ጎዳና ዳር ቆመህ የሴቶችን ዳሌ በማወዳደር ነውን? ተው ተመከር ተው! አለም አላፊ ነው፤ መልክ ረጋፊ ነው፤”ብሎ ተከዘ። እኔም መልሼ፤”ስማ! አለምማንበብ ይቀጥሉ…

ከተረቶች ጀርባ “አበው”

ልጅ እያለሁ ጅብ እና ሌባ አንድ ይመሱሉኝ ነበር። “ጅቡን እንዳልጠራው!”፣ “ሌባው ይሰርቅሃል!”… እየተባልኩ ነው ያደኩት። ጅብንም ሆነ ሌባን አይቻቸው አላውቅም ነበር። እንድፈራቸው ሲባል ብቻ የተሰገሰጉብኝ እሳቤዎች ግን አንድ አይነት አስፈሪ ምስል ፈጥረውብኝ ስለነበር ሌባም ሆነ ጅብ አንድ ነበሩ። አድጌ ነገሮችንማንበብ ይቀጥሉ…