ሥግር ልብ ወለድ፤ ሕፅናዊነት (ክፍል 3)

 ‘እንካነት’ አፍ ለንባብ ወደ አደባባይ ከመምጣቱ በፊት፤ ደራሲው ለአምስት ወንድም ደራሲዎች የመፅሀፉን የተተየበ ኮፒ በመስጠት ሥግር እንዲሰሩበት ጋብዞ ነበር። የደረሱኝን እነዚህን ሥግሮች በአፍ ሁለተኛ ዕትም ላይ እንደማቀርብ ተስፋ አደርጋለሁ። ‘እንካ’ ብዬ የምጠራውም ይህን ደራሲያኑን የመጋበዝ ድርጊት ነው። አፍ የተባለውን ይሄንማንበብ ይቀጥሉ…

አይደለም ምኞቴ

አይደለም ምኞቴ ለምለም አንገትሽ ላይ : ክንዶቼን መጠምጠም ዳሌሽ ላይ መንሳፈፍ: ጭንሽ ማሃል መስጠም እይደለም ምኞቴ ከንፈርሽን ማለብ ቀሚስሽን መግለብ ከገላሽ ቆርሼ :ገላየን መቀለብ ደረትሽን ማለም ጡትሽን መሳለም በቁንጅናሽ ጅረት : ገነቴን ማለምለም አላማየ አይደለም:: ምኞቴን ልንገርሽ? ካለሺበት ቦታ: ቀልቤንማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹የዞረ ድምር››

(መነሻ ሃሳብ- ሴክስ ኤንድ ዘ ሲቲ ተከታታይ ፊልም) ደንበኛ ፍቅር በጀመርን በአራተኛው ሳምንት ይመስለኛል፣ በሰበብ ባስባቡ ሲያከላክለኝ ቆይቶ በመጨረሻ ቤቱ ይዞኝ ሄደ። – የወንደ ላጤ ቤት ነው እንግዲህ…ያልተነጠፈ አልጋ አየሁ፣ ያልታጠበ ካልሲ ሸተተኝ ምናምን ብለሽ እንዳትተርቢኝ አለ እጄን ይዞ የአፓርትማውንማንበብ ይቀጥሉ…

ሥግር ልብ ወለድ፤ ሕፅናዊነት (ክፍል 2)

“ነው” ተብሎ ቢደነገግም ባይደነገግም ማንኛውም ልብ ወለድ ሥግር ነው። ማለት የራሱን ጉጥ/ዐይን መርጦ የራሱን ሥግር ይሰራል። የየራሱን አቋምና ልዩነት ይደነግጋል። ልዩነት ሲባል ሂደት ማለት ነው። ስለዚህ አፍ ሥግር ነው ብዬ በንዑስ ርዕስ መጥቀሴ ስለ ነጠላ ዕቅዴ ይናገራል እንጂ ስር ነቀልማንበብ ይቀጥሉ…

ከሚነሶታ እስከ አዲስ አበባ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የአሜሪካ ጉብኝታቸውን ፈጽመው ወደ አዲስ አበባ የሚመለሱበት ሰዓት ላይ ደርሰናል። ልዑካኑ በሁለት ተከፍለን ነበር ከሆቴል ወደ አውሮፕላን ማረፊያው የሄድነው። የመጀመሪያው ቡድን ከጠዋቱ 4፡30 ሲነሣ፤ ሁለተኛው ቡድን ደግሞ 6፡15 ላይ ከሆቴል ተነሣ። አስቀድመን ለመነሣት ያሰብነው ከጠዋቱማንበብ ይቀጥሉ…

ተፈጥሮን ደጅ ልጥና

” እኔ ልሙትልሽ” እያልኩኝ አልምልም ቃላቴን መንዝሬ: ለሞት ቀብድ አልከፍልም ያኔ ትዝ ይልሻል? “ራስህን ግደል” ብለሽ በረኪና የላክሽልኝ ጊዜ እድሜ ለስጦታሽ: ታጠበ ሸሚዜ። ገደብ ጫፍ በሌለው: በልቤ መጋዘን ቢታጨቅ መከራ: ቢጠራቀም ሀዘን “ባለፈልኝ” እንጂ “በሞትኩ” ብየ አላቅም ካልጋ ላይ ነውማንበብ ይቀጥሉ…

ኢትዮጵያዊ ነን!

ፈቅደን ሲመሩን፤ ችቦ ተቀባይ ለሚነዱን ግን ፤ አሻፈረን ባይ ካልነኩን በቀር፤ ቀድመን ማንዘምት ከጋሻ በፊት ፤ ጦር የማንሸምት ኢትዮጵያዊ ነን! ህብር ያስጌጠው፤ ህይወት ለማብቀል ዘር ሳናጣራ ፤ የምንዳቀል ለነዱን ሰይጣን፤ ለመሩን ሰናይ ጌታን ከገባር፤ ለይተን ምናይ፤ ኢትዮጵያዊ ነን! ብዙ ህልሞችን፤ማንበብ ይቀጥሉ…

ስግር ልብወለድ፣ ሕጽናዊነት (ክፍል 1)

‘I see the world in a grain of sand And a heaven in a wild flower…. ‘ (1803) እንግሊዛዊው ገጣሚ ዊሊያም ብሌክ የሰፈራችን ልጅ ቴንሳ እንዲህ የሚል ግጥም አለው፤ ‘አለምን በደቃቃ ጤፍ አያታለሁ አገሬንም በቁራሽ እንጀራ’ የዋህነት እንዴት ያደክማል? ከተባለውማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹ቦግ – እልም›› 

ቅድም ባንክ ሄጄ ነው። የሚመለከተኝን ቅፅ ሞልቼ ከደብተሬ ጋር ወረፋ አስያዝኩና ሊሞላ አንድ ሰው በቀረው አንዱ አግዳሚ ላይ ተቀመጥኩ። ከመቀመጤ መብራት ሄደች። ‹‹ኤዲያ! ምን ጉድ ነው …አሁንማ ባሰባቸው….›› አሉ አጠገቤ የተቀመጡት ሰውዬ። ሙሉ ልብስ ካለ ከረቫት የለበሱ፣ ባርኔጣ ያጠለቁ ስልሳዎቹማንበብ ይቀጥሉ…

‹‹እኔን ነው?››

ገና እምቦቃቅላ ሳለሁ፣ አባቴ ..‹‹ጠይም ልጅ ባይኔ ላይ ተሸክሜ እንደኩል›› እያለ ጥቁረቴን የሚያወድስ ዘፈን ይዘፍንልኝ ስለነበር ከኩል የተሰራሁ ይመስለኝ ነበር። ከኩል ስለተሰራሁ ፣ ገና ልጅ ሳለሁ ኩል መኳል ያጓጓኝ ስለነበር አባቴ በእሱ ሃገር ሴት ልጅ የምትኳለው ልትዳር ስትል እንደሆነ እያጫወተ፣ማንበብ ይቀጥሉ…