ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት… እኔ የቀጠልኩት (ክፍል አንድ)

«ሞቼ ቢሆን ኖሮ ደስ ይልሽ ነበር አይደል?» አለኝ በወጉ ማሽከርከር ያልለመደውን ዊልቸር እየገፋ ወደሳሎን ብቅ እንዳለ። ፊቱ ምሬት ወይ ጥላቻ በቅጡ ያልለየሁት ስሜት ይተራመስበታል። ዝም ያልኩት መመላለሱ ልቤን ስለሚያደክመኝ ነበር። በጎማው እየተንቀራፈፈ አጠገቤ ደርሶ « ንገሪኛ ደስ ይልሽ ነበር አይደል?»ማንበብ ይቀጥሉ…

ሠማየ ውድውድ (ምዕራፍ፡፫)

እና፥በእዚህ፡አስደናቂ፡ጎዞ፡ወቅት፡ነው፥ለተረት፡የማይመስል፣ለዕውን፡የሚያስፈራ፣ለግምት፡የቸገረ፡`ኣጋጣሚ`፡ከፊት፡ለፊታችን፡የተደቀነብን።የሆነው፡ስለ፡ሆነ፡እና፤መዝገብ፡የሙያ፡ግዴታዬ፡በመሆኑም፤አነሆኝ፤ገጠመኙን፡እንደሚከተለው፡ከትቤዋለሁ።ትርጉም፥የግል፣ዕምነትም፡የተጸውዖ፡ናቸው፡እና፥እንደመሰላችሁ፡ተረዱት።ማንበብ ይቀጥሉ…

የቀይ ልክፍት

 “ጥሬ ስጋ በቀይ ወይን ምሳ ልጋብዝሽ” ብሎ ነው የጀመረኝ። “በደስታ” አልኩኝ። ጥሬ ስጋ ነፍሴ እንደሆነ ማንም ያውቃል።…… “ምሳ በልቼ አሁን መጣሁ” ብዬ ከቤት ወጥቼ የሚቀጥለውን ቀን ምሳ በልቼ ተመለስኩ። በቁርጥ ሰበብ ስንቋረጥ ዓመት ሆነ።…… “ሜዬ ገብቶልሻል ይሄ ልጅ! “ይሉኛል ጓደኞቼ……ማንበብ ይቀጥሉ…

ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው!! (ክፍል ሁለት)

የሳመኝ ቀን “በናትህ ይሄን ነገር በምስክር ፊት አድርግልኝ” ብለው ደስ ባለኝ። ስሜ መራራ ነዋ። ሳመችው እንጂ ሳማት አይባልልኝማ! እርግጥ የሳመኝ እለት ያልኳችሁ ቀን ማለት በዋዛ የተገኘ እንዳይመስላችሁ “ጌታ ሆይ ይሄ ሰው በወንድምነት ይሁን በባልነት ፍቅር የሚወደኝ መለየት የምችልበት ፀጋ ስጠኝ!ማንበብ ይቀጥሉ…

ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው!!

ግርምታችሁን እና እርግማናችሁን ከማዥጎድጎዳችሁ በፊት ትንፋሽ እየሰበሰባችሁ ከመጀመሪያው ልጀምርላችሁና ሁለቱንም ላስተዋውቃችሁ። የመጀመሪያው ባሌ “ባለቤቴ ነው ተዋወቂው!” ብዬ ያስተዋወቅኳት ጓደኛዬ “ወየው በፈጣሪ ባልሽ ሲያምር አጣብሺኝ!” ያለችለት ውብ ነው። የገዛ እናቴ ልክ እንደጠበስኩት ስታውቅ “ውይ ልጄ የልጁን ህይወት አታበልሺ አጉል ታደርጊዋለሽ !ይቅርብሽማንበብ ይቀጥሉ…

አልወዳትም እንጂ አልጠላትም (ክፍል 10-11)

(በተጋባዥነት) ክፍል 10 ማን እንደሆነች አላወቅኩም።ለምን “ማቲ” ብላ ስሜን እንደወዳጇ እንዳቆላመጠችኝ ጭምር። ደግሞስ እንደሷ ያለችን ቆንጆ ለመወዳጀት የሚያበቃ ወኔ ከየት አግኝቼ? ደግሞስ ኤዶምን የምታውቃት ከሆነ አሁን “ማቲ” መሆኔን ካመንኩላት ለእህቴ ተናግራ ልፋቴን ሁሉ ገደል ብትከተውስ?”ይቅርታ የኔ እህት ተሳስተሻል ማቲ አይደለሁም”ማንበብ ይቀጥሉ…

አልወዳትም እንጂ አልጠላትም (ክፍል 8-9)

(በተጋባዥነት) ክፍል 8 በቀጣዩ ቀን በጠዋት ተነሳሁ። የERAን ‘Divano’ የተሰኘ ሙዚቃ እየሰማሁ በሞቀ ውሀ ሰውነቴን አስደበደብኩ።ሙዚቃውና የውሀው እንፋሎት ተደማምሮ የሆነ ስርየት የመስጠት ስሜት አለው። እንደከባድ ፀሎት ሁሉ ልቤ ፍርስ ይላል።ከየት እንደመጣ የማላውቀው የእጣን ሽታ አፍንጫዬን ያውደዋል።ልቤ ወደህፃንነቴ ይሸፍትብኛል። ደጓ አክስቴማንበብ ይቀጥሉ…

አልወዳትም እንጂ አልጠላትም (ክፍል 6-7)

(በተጋባዥነት) ክፍል 6 ከለቅሶው ድንኳን ባሻገር ቁጭ ብዬ በግድ የምታለቅሰዋን ትንሿን እህቴን አያታለሁ። “ኤዱዬ አይዞሽ!” ብለው በደጋገፏት ሰዎች መሀል ሆና ፊቷ ላይ የማየው ህይወት አልባነት እናታችንን አስታወሰኝ። ለመጨረሻ ግዜ እናቴን ያየኋት የሞተች እለት ነበር።የአስራ አራት አመት ጎረምሳ ሆኜ። የመጀመሪያም የመጨረሻምማንበብ ይቀጥሉ…

አልወዳትም እንጂ አልጠላትም (ክፍል አምስት)

“ኤደን ምን ይሰማሻል?” “ምንም” (ዝም ተባብለን ሰዓቴ አልቆ እመለሳለሁ::) በሌላኛው ቀንም …….. “ኤደን ዛሬስ ለማውራት ዝግጁ ነሽ?” “አይደለሁም!! ማውራት አልፈልግም!” (ዝምምምምም….. ሰዓቱ ያልቃል) ደግሞ በሌላኛውም ቀን “ኤደን ዛሬስ ለመጀመር ዝግጁ ነሽ?” “ምኑን?” ” ማውራት ትፈልጊያለሽ?” “እኔ ምንም የማድረግ ፍላጎት የለኝም!!”ማንበብ ይቀጥሉ…

አልወዳትም እንጂ አልጠላትም (ክፍል አራት)

‘ከቤቴ ውጪልኝ’ የሚለውን ዘላ ‘ከህይወቴ ውጪልኝ’ ያልኳትን ሰምታኝ መሰለኝ……. የሞተችው…… “ኤዱዬ የኔ ከህይወትሽም ከቤትሽም መውጣት አንቺን አያስተካክልሽም!! Let us make this right!! ላግዝሽ?” አለችኝ …. “የቱን? የቱን ነው የምናስተካክለው?” አልኳት “ያንቺ እህት አለመሆኔን? ንገሪኝ ከየት እንጀምር? ገና ሳልወለድ ቤተሰቦችሽ ከከዱኝ?ማንበብ ይቀጥሉ…