ማምሻውን ነው። ዝናብ ያረሰረሰውን የሰፈራችንን ኮብልስቶን መንገድ በጥንቃቄ እየረገጥኩ ወደ ቤቴ አዘግማለሁ። በድንጋዮቹ መሃከል የፈሰሰው ውሃ በረገጥኩት ቁጥር ፊጭ ፊጭ ይላል። ዘንቦ ማባራቱ ስለሆነ ይበርዳል። ፊጭ ፊጭ እያደረግኩ መራመዴን ስቀጥል፣ ከዚህ በፊት አይቼ በማላውቀው ሁኔታ በመንገዴ ላይ ከሰል አቀጣጥለው፣ በቆሎማንበብ ይቀጥሉ…
አብይ አህመድ (ዶክተር) በ “ፈርዖን” ፊት
ከአንድ ዓመት በፊት፣ ‹እርካብና መንበር› በሚል ርዕስ፣ ‹ዲራአዝ› በሚል ደራሲ ስም የወጣ መጽሐፍ ላይ እንዳነበብነው፣ መሪነት ድንገት ላያችን ላይ የምንጭነው አክሊል፣ ወይም እግረ መንገዳችንን እንደ ዘበት አንስተን የምናጠልቀው ቆብ መሆን የለበትም ።ስንመኘው፣ ስንጠብቀው፣ በትንሹ ስንለማመደው የነበረ፣ ለራሳችን የምናበረክተው፣ የምንፈተንበት፣ እኛንማንበብ ይቀጥሉ…
የኬዱክ እጆች
( ማሳጅ በባሊ፣ ኢንዶኖዢያ) -የቱሪስት ሃገር ስለሆነ ኑሮ እሳት ነው…እኔ ደግሞ ደሞዜ በጣም ትንሽ ነው። በወር ሁለት ነጥብ ሶስት ሚሊዮን ይከፍሉኛል ግን አይበቃኝም…የቤት ኪራይ ዘጠኝ መቶ ሺህ እከፍላለሁ… ኬዱክ ናት እንዲህ የምትለኝ። ኬዱክ በስመጥሩ ሆቴል ውስጥ ያለ ዝነኛ የስፓ አገልግሎትማንበብ ይቀጥሉ…
”የቱ ይበልጣል?“
ዛሬ ነው። የቀጠርኩት ሰው እስኪመጣ ፣ ከከተማችን ቅንጡ የገበያ ማዕከሎች በአንዱ ውስጥ ያለ ግብ እዞራለሁ። ለድሪቶነት ለሚቀርብ ሱሪ የሃምሳ ኪሎ ጤፍ ሂሳብ የሚያስከፍሉ ሞልቃቃ ቡቲኮች። ርካሹ ኬክ በ 40 ብር የሚሸጥባቸው ካፌዎች። አምስት ካሬ የማይሞላ የቄንጠኛ የግድግዳ ወረቀት ጥቅልን በሺህማንበብ ይቀጥሉ…
ከእንቅልፍ መልስ…
[ዳንሱን ከዳንሰኛው መነጠል ይቻላልን?] ___ ስለ ማንነት ሲነሳ በመስታወት ውስጥ ‘ፊቱን’ እያየ የሚመሰጥ ሰው ነው በዓይነ ሕሊናዬ የሚታየኝ… የናርሲስ ቢጤ … ናርሲስ በግሪክ ሚቲዮሎጂ ገጾች በውሃ ውስጥ የሚያየውን ምስል ለማምለክ ጥቂት የቀረው ሰው ሆኖ ተስሏል… በማንነት ጉዳይ ሁላችንም ናርሲስት ነን…ማንበብ ይቀጥሉ…
ባለ ከረሜላው ሰውዬ
ቢሮ ሆኜ ከስራ ፋታ ሳገኝ ማረፊያዬ ዩ ቲዩብ ነው። የድሮ ዘፈን እየጎረጎርኩ አዳምጣለሁ። ዛሬ ጠዋት የ80ዎቹ እና 90ዎቹን አር ኤንድ ቢ ሙዚቃዎች እየሰማሁ ሳለ የልጅነት አእምሮዬ ላይ ተነቅሶ ከቀረ አንድ ዘፈን ጋር ተገናኘን። ርእሱ ‹‹ካንዲ ሊከር›› ዘፋኙ ማርቪን ሴስ ይባላል።ማንበብ ይቀጥሉ…
“ይሸታታል”
ለምኖርበት ህንፃ የፅዳት ተጠሪ ስለሆንኩ በየወሩ እየዞርኩ ለሠራተኞች የሚከፈለውን ደሞዝ መዋጮ እሰበስባለሁ። ቅዳሜ እንደተለመደው እየዞርኩ የአንዷን ጎረቤቴን አፓርትማ አንኳኳሁ። ከፈተች። ከእሷ ቀድሞ ከቤቷ ውስጥ የወጣው ትኩስ እንጀራ ሸታ አወደኝ። የትኩስ እንጀራ ነገር አይሆንልኝም። ቁንጣን ይዞኝ ‹‹ማር እንኳን አልልስም›› ብዬማንበብ ይቀጥሉ…
March 8 – ሴቶች የሚነቆሩበት ቀን
አንድ አድራጎት አስደማሚ የሚሆነው አድራጎቱ በዓለም ላይ “የመጀመሪያ” ሲሆን አልያም የአድራጊው ድርጊቱን መፈጸም ከአዕምሮ በላይ ሲሆን ነው… የኖረና የነበረን ጉዳይ እጹብ ድንቅ አድርጎ መሸላለም ግን አንድም ለአድራጊው የተሰጠን ዝቅተኛ ግምት አልያም ድርጊቱን ለማመናፈስ የተደረገን ጥረት ያሳያል… ___ አውሮፕላን በሴቶች ሲበርማንበብ ይቀጥሉ…
Connecting the dots
ልጅ እያለሁ ነጥቦችን በማዋደድ ጨዋታ እዝናና ነበር… በአንዳንድ ጋዜጣና መጽሔቶች የጀርባ ገጽ ላይ በተንተን ያሉ ጥቂት ነጠብጣቦች ይቀመጡና አንባቢያን በነጠላ መስመር ሲያገናኟቸው አንዳች ትርጉም ያለው ቅርጽ እንዲሰጡ ሆነው ይታተማሉ… ነገሩ መዝናኛ ቢሆንም አስተውሎ ላየው አንዳች እውነት ሹክ ማለቱ አይቀርም… ትላልቅማንበብ ይቀጥሉ…
የኔ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ!
ነፃነት ያልነካው ትዳር እና ሀገር መፍረሱ አይቀርም ብዬሻለሁ። አልሰማሽም። አለመስማት የአፍራሾች ምልክት ነው። የማይሰሙ መንግስታት ሀገራቸውን፣ የማይሰሙ ባለትዳሮች ትዳራቸውን ያፈርሳሉ። የቤቴ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ነሽ። ሲበዛ ትጠረጥሪኛለሽ። ጥርጣሬሽን ለማረጋገጥ ንብረቶቼን ያለፍቃዴ ትበረብሪያለሽ፣ ልብሶቼን ትፈትሻለሽ፣ ቴክስቶቼን ከፍተሽ ለማንበብ ትሞክሪያለሽ። የአስቸኳይ ጊዜማንበብ ይቀጥሉ…