ያኔ …ከዛ ከኛ ቤት ከባሰ አመዳም ደሃ ጎረቤታችን ቦቸራ ሳረግዝ…… ለአባዬ ውርደቱ ሆንኩ። በየሴሚስተሩ አንደኛ እየወጣች ስሙን የምታስጠራው ልጁ በአንድ ቀን ስህተት አፈር ከድሜ ገባች። … ወራት ነጎዱ… ትምህርቴን ከ11 ተውኩት። ልጄን ገጠር አክስቴጋ ሄጄ ወለድኩ።…… የአባዬ ውርደት የነበረው ሌባውማንበብ ይቀጥሉ…
ጠብታ ማር እና ጠብታ ስብከት
ሊዎ ቶልስቶይ የሚወዳት አንድ የምስራቃውያን ተረት አለች፤ በጣም አሳጥሬ ሳቀርባት ይህን ትመስላለች’ የሆነ ሰውየ የሆነ ቦታ ሲሄድ አንበሳ አባረረው ፤ ሮጦ ዛፍ ላይ ወጣ ፤ የዛፉ ቅርንጫፍ እባብ ተጠምጥሞበታል፤ ሰውየ ዝቅዝቅ ሲያይ ከዛፉ ስር ሀይቅ ተመለከተ፤አንድ ግብዳ አዞ አፉን ከፍቶማንበብ ይቀጥሉ…
ሞካሪና አስሞካሪ
(ማስጠንቀቂያ …. አልባሌ ነገር የማትወዱ ሰዎች አታንብቡ … ኡኡኡኡኡ .. 🙆🏻♀️🙆🏻♀️ይሄን አልፋችሁ ካነበባችሁ እንዳትመክሩኝ) “ከንፈር መሞከር ፈልጋለሁ።” አልኩት “እስከዛሬ ተስመሽ አታውቂም።?” “እስከዛሬ ፈልጌ አላውቅም።” ከንፈሩን አቀበለኝ። ወራት ነጎዱ…… “ድንግል መሆን አልፈልግም።” አልኩት “ገናኮ 18 ዓመትሽ ነው ማሬ። ለምን ትንሽ አንቆይም?ማንበብ ይቀጥሉ…
ከ”መግባት እና መውጣት” የተቀነጨቡ አንቀፆች
ምኡዝ እንዲህ አለ 1 “ የሰው ልጅ ተገንጣይ እንስሳ ነው፤ ባለፈው አንዱ “ የአዲሳባ ልጅ” የሚል ፅሁፍ ያለበት ቲሸርት ለበሰ፤ ወድያው ብዙ ሰዎች እንደሱ መልበስ ሲጀምሩ ተገንጥሎ “ የሽሮ ሜዳ ልጅ “ የሚል ፅሁፍ ያለበት ቲሸርት ለበሰ፤ ብዙ የሰፈር ልጆችማንበብ ይቀጥሉ…
ሕልሜን አደራ
(ዊልየም የትስ Cloths of heaven ብሎ እንደፃፈው) በእውቀቱ ስዩም ወደ አማርኛ እንደመነዘረው ) ባይመረመሬ ጥበብ ተሽቀርቅሮ ከወርቃማ ብርሃን፤ ከብርማ ፀዳል የተሰራ ሸማ፥ ማግኘት ብችል ኖሮ ከውብ እግሮችሽ ስር፥ እዘረጋው ነበር ግና ምንም የለኝ፥ ከህልሞቼ በቀር ፡፡ የኔ ውድ እንግዲህ ሕልሜንማንበብ ይቀጥሉ…
የቋንቋ ነገር
ለአዲሳባ ከንቲባነት ልወዳደር ወይስ ለክቡር ገና ልተውለት? ምን ያንሰኛል? ሌላው ቢቀር ሁለት ቋንቋ እችላለሁ – የአራዳና የገጠር አማርኛ አቀላጥፌ እናገራለሁ፤ የዛሬ አመት ገደማ ይመስለኛል: በካፒታል ሆቴል ጀርባ ባለው አቋራጭ መንገድ ሳልፍ ሁለት ጎረምሶች ይተናነቃሉ፤ ገባሁና ገላገልኩ፤ ሳጣራ አንዱ በቅርቡ ከታክሲማንበብ ይቀጥሉ…
እኔኮ አንጀቴን የሚበላኝ….
አሜሪካ ውስጥ በየቀኑ የማይደረግ አይነት ሰልፍ የለም! በዚህ ሁለት ሳምንት እንኳን ሁለት ሰልፍ አይቻለሁ። ኢራቃዊያን የአሜሪካን የአየር ድብደባ ተቃውመው የወጡትን ሰልፍ በመንገዴ አየሁ …የበርማን መፈንቅለመንግስት አለም ቸል ብሎታል የሚሉ በርማዊያንም ባለፈው ቅዳሜ ተሰልፈው የሆነ ዩኒቨርስቲ በር ላይ ሲጮሁ አየሁ! እዛማንበብ ይቀጥሉ…
ዶሮዎች ለእኛ ምን አደረጉ ብላችሁ ከመጠየቃችሁ በፊት
ዶሮዎች ለእኛ ምን አደረጉ ብላችሁ ከመጠየቃችሁ በፊት፥ እኛ ለዶሮዎች ምን አደረግንላችው ብላችሁ ጠይቁ፤ በቀደም አንዱ ጉዋደኛችን ሊያገባ እጮኛው ቤት ሽምግልና ተላክን ገና ገብተን ወንበራችን ላይ ሳንደላደል “ ልጁ ምን አለው?” አሉ አባትየው ፤ ከጉዋደኞቻችን አንዱ ኮራ ጀነን ብሎ መለሰ፤ “ልጁማንበብ ይቀጥሉ…
ስለትግራይ ሲነሳ ብዙ ይነሳል
እኔ ጭሮ አዳሪ ስለሆንኩ መጀመርያ የማስታውሰው የፅሁፍ ሰዎችን ነው፤ አለቃ ተወልደ መድህን ፤ ደብተራ ፍስሀ ወልደጊዮርጊስ ፥ ገብረህይወት ባይከዳኝ ፤ ስብሀትለአብ ገብረእግዚአብሄር ፥ ከትግራይ ምድር የተሰጡኝ የኢትዮጵያ ገፀበረከቶች ናቸው። ከ ሶስት መቶ አመት በፊት የተፃፈ የታሪክ ድርሳን አግኝተህ ብታነብ ትግራይማንበብ ይቀጥሉ…
ምርመራ
በቀደምት ቴክሳስ ከተማ የበረዶ ውሽንፍር ጥሎ የከተማው መብራት ተቁዋረጠ፤ በማግስቱ የከተማው አስተዳዳሪ ደውሎልኝ ለከተማው ህዝብ ልምድ እንዳካፍል ጋበዘኝ። “ያለመብራት የመኖር ጥበብ“ እሚል ጥናታዊ ፅሁፍ አዘጋጀሁና ናሙናውን ላክሁለት፤ በጣም ተደስቶ መጠኑን እዚህ ገፅ ላይ የማልገልፀውን ቀብድ ላከልኝ ፤ በህይወቴ ለመጀመርያ ጊዜማንበብ ይቀጥሉ…