ንጉሥ መሆን 2

እንደ ካሊጉላ ዓይነት መንፈስ ላለው ንጉሥ መሆን ሥራው አልያም: ደግሞ የ’ለት እንጀራው ማለት ነው። ግና ንጉሥ መሆን ያልፋል ይራመዳል ከዕለት እንጀራነት ንጉሥ መሆን ያልፋል ከስም ማሥጠርያነት ይልቅ ያሥፈልጋል አብነት ሊያደርጉት የዘርዓ ያዕቆብን ቆራጡን ልብ ኣይነት ፍት’ እንዳይሣሣት በልጅ ላይ ጨክኖማንበብ ይቀጥሉ…

ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያዊነት፣ ሀገር ግንባታ

የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ‘ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በአማርኛ ሥነ ፅሁፍ’ በሚል ርዕስ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ተባባሪ ፕሮፌሰር ቴዎድሮስ ገብሬ፤ የጸጋዬ ገብረመድህንና የአዳም ረታን ስራዎች ዋቢ በማድረግ ስለ ብሔርተኝነትና ሀገር ግንባታ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል። የጥናታዊ ፅሑፉ ጨመቅ (Summary) ለንባብ እንዲመች ተደርጎ እንደሚከተለው ቀርቧል።ማንበብ ይቀጥሉ…

‘እዬዬ ሲደላ ነው’ ይላሉ

‘እዬዬ ሲደላ ነው’ ይላሉ። ተረቱን ያመጣሁት፤ ደንባራ የሆነ የባዕድ ባህል ቅጂ ምን ቦታ እንደሚከተን ሳስብ እያለሁ፤ ‘ሙሾ አውራጆች የኋላ ቀር ባህል እሴቶች እንደሆኑ’ ሊነግረን የሚጥር፣ በምርምር ያልተደገፈ፣ ጥልቅ በሆነ ፍልስፍና ሞትን፣ ሃዘንና ኪነትን እንድንረዳ ለደቂቃ እንኳን ያልጣረ፣ ለስሙ ‘ለኪነ ጥበብማንበብ ይቀጥሉ…

ጠብታ ማር እና ጠብታ ስብከት

ሊዎ ቶልስቶይ የሚወዳት አንድ የምስራቃውያን ተረት አለች፤ በጣም አሳጥሬ ሳቀርባት ይህን ትመስላለች’ የሆነ ሰውየ የሆነ ቦታ ሲሄድ አንበሳ አባረረው ፤ ሮጦ ዛፍ ላይ ወጣ ፤ የዛፉ ቅርንጫፍ እባብ ተጠምጥሞበታል፤ ሰውየ ዝቅዝቅ ሲያይ ከዛፉ ስር ሀይቅ ተመለከተ፤አንድ ግብዳ አዞ አፉን ከፍቶማንበብ ይቀጥሉ…

‘The past is a foreign country’ (ያለፈው ዘመን ባዕድ አገር ነው)

ይሄን የእንግሊዝኛ ተረት በዚህ ዓመት ውስጥ ሺህ ጊዜ ሳልሰማው አልቀርም። ግን መደጋገሙ ሲበዛብኝ፤ አባባሉ እንዲወደድ ስልት ያለው የማለማመጃ ዘመቻ ወጣቱ ላይ እየተሰራ መሰለኝ። ዘይቤውን የሚናገሩት ብዙ የጥቁር ሀበሻ (ሀበ) ፈረንጃዊያን ብቅ ብለዋል። እነሱም ʻየአገራችንን መልካም ታሪክ እንጥቀስʼ ስንል ዐይኖቻቸው ቀልተውማንበብ ይቀጥሉ…

አንዳንዴ

ባልተገራ ፈረስ በፈጣን ድንጉላ ኑሮን ባቦ ሰጠኝ ህይወትን በመላ በዚህ በኩል ሲሉህ ንጎድ ወደ ሌላ፤ እስከመቼ ድረስ ዳር ዳሩን መራመድ ፤ በጭምት ሰው ስሌት በክብር ካልመጣ፤ ሞክረው በቅሌት ሰው ቅፅር አይደለም፤ በእሾህ የታጠረ እንድትጥሰው ነው፤ ህግ የተፈጠረ። አይሰለቺህም ወይ መኖርማንበብ ይቀጥሉ…

ለሙዚቃ የመነነው ኤሊያስ!

  በዓሉ ግርማ ከሀዲ ደራሲ መሆኑን የነገረኝ የቀድሞ መምህሬ ቴዎድሮስ ገብሬ ነበር።“ከአድማስ ባሻገርን” ካነበብኩ በኋላ እኔም የእሱ ጭፍራ ሆንኩኝ። ታላቁን ደራሲ በክህደት ወነጀልኩኝ። ተስፋ ያጣውን አበራ ወርቁ ለምን ሲል በልቦለዱ መቋጫ ላይ በጉልበት ብሩሽ አስጨብጦ ከብርሃን አገናኘው አልኩኝ። ፍርሃቱን እረገምኩኝ።ማንበብ ይቀጥሉ…

ኤልያስ፡- ሀገር ነው እኖርበታለው!

የጌቴ አንለይ፥ የቀይ ጥቁር ጠይም፣ የቤሪ፥ ሕሊና እና የልዑል ኃይሉ፥ አንቺ ነሽ አካሌ ዘፈኖች በቁጥር ሶስት ቢሆኑም፥ በመንፈስ አንድ ናቸው። ከኢትዮጵያዊው ኤልያስ ማህፀን የተማጡ። ወንዱ ኤልያስ ወላድ ነው፥ ያውም ልበ መልካሞችን የሚወልድ። እያንዳንዳቸው ዘፈኖች ብቻቸው ቁመው መነበብ ቢችሉም፥ ሶስቱም ገምደንማንበብ ይቀጥሉ…

‘’ኤልያስ መልካ-ኒዝም’’

እመነኝ ጥበብን አታሳድጋትም ፤ በጥበብ ውስጥ ግን አንተ ታድጋለህ። የፈላስፋነት እና ፍልስፍና ትርጉምም ‹‹ምላሽ መፈለግ›› ነው። ኤልያስ መልካም በጥበብ ፍለጋው የ‹‹ለምን›› ጥያቄዎች አጭሮ ታገኘዋለህ። የቤትሆቨንም ምክር ይህ ነው፡- ‹‹Don’t only practice your art, but force your way into its secrets››ማንበብ ይቀጥሉ…

ሃሳብ አትሞትም(ሶስት ታሪኮች)

በመካከለኛው ዘመን በመላው አውሮፓ መንግስት የነበረችው የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ናት። ቤተክርስቲያን አምባገነን ነበረች። በሃይማኖት ስም ታስራለች ፣ ታሰቃያለች ፣ ትገድላለች። ሳይንስ ተቀባይነት ያለው ከሃይማኖቱ አስተምህሮ ጋር ስሙም ሲሆን ብቻ ነው። ከዚያ በተረፈ አዳዲስ ሃሳቦች ብቅ ካሉ መልሳ ትቀብራቸዋለች። ሶስት ታሪኮችን እንይ፦ማንበብ ይቀጥሉ…